04/07/2022
ማቲያስ ዴ ላይት ከቼልሲ ይልቅ ባየር ሙኒክን ይመርጣል !
እንደ ስካይ ጀርመን ዘገባ ከሆነ ባየር ሙኒክ ማቲያስ ዴ ላይትን ማስፈረም ይፈልጋሉ።
ዴ ላይት ከ ናግልስማን እና ከክለቡ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግሯል በዚህም ንግግር 22 አመቱ ተከላካይ ደስተኛ ነበር ተብሏል።
ቼልሲ እና ሌሎች ክለቦች ፍላጎት ቢኖራቸውም ዴ ላይት በአያክስ ቆይታው እንኳን እሱን ለማስፈረም ፍላጎት ለነበረው ለ ጀርመኑ ክለብ መፈረም ይፈልጋል።
ባየር ሙኒክ ከጁቬንቱስ ጋር ግንኙነቶችን ጀምሯል ድርድር ጥሩ እድገት ቢኖረውም ለተጫዋቹ ጁቬንቱስ ከፍተኛ ገንዘብ ስለሚፈልጉ ዝውውሩን አስቸጋሪ ያደርገዋል።
ቼልሲዎች ዴ ላይትን ለማስፈረም ወደ ኃላ አይሉም ምክንያቱም ባየርን ሙኒክ ለተጫዋቹ ከፍ ያለ ወጪ እንደማያወጣ ያምናሉ።
ሆላንዳዊው ተከላካይ ወደ ሙኒክ መሄድን ይመርጣል እና ሁለቱ ክለቦች ስምምነት ላይ እንደሚደርሱ ተስፋ አድርጓል።