07/11/2025
ሄንደርሰን ብሬንትፎርድን ሊቀላቀል ተስማማ!
እንግሊዛዊው አማካይ ጆርዳን ሄንደርሰን የፕሪምየር ሊጉን ክለብ ብሬንትፎርድን ለመቀላቀል ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል። ከአያክስ ጋር መለያየቱን ተከትሎ ኮንትራት የሌለው ሄንደርሰን፣ ብሬንትፎርድን በነፃ ዝውውር ይቀላቀላል።
የ35 ዓመቱ አማካይ ሄንደርሰን ወደ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ በመመለስ የሁለት ዓመት ውል እንደሚፈርም ተነግሯል። ሌሎች የዝውውር አማራጮች ቢቀርቡለትም፣ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ለመመለስ በመወሰኑ ብሬንትፎርድ ዝውውሩን ለማጠናቀቅ ተቃርቧል።
የዝውውሩ ሂደት ቢጠናቀቅም፣ ጆርዳን ሄንደርሰን ለቀድሞ የቡድን አጋሩ ዲያጎ ጆታ ክብር ዝውውሩ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋ እንዲደረግ መጠየቁ ተዘግቧል።
ይህን እና ሌሎችንም አዳዲስ የስፖርት ዜናዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ: https://t.me/+Oe6AIBLwdZE0MDNk