Woldia Sport Club New Page 2013 E.C

Woldia Sport Club New Page 2013 E.C ወልድያ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት እንዲጫወት

የኢሚግሬሽን የዜግነት አገልግሎት ምዝገባ በከተማው መጀመሩ ከእንግልት አድኖናል ሲሉ ተጠቃሚዎች ተናገሩ። የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በወልድያ ከተማ ስራ መጀመሩ ካ...
13/03/2026

የኢሚግሬሽን የዜግነት አገልግሎት ምዝገባ በከተማው መጀመሩ ከእንግልት አድኖናል ሲሉ ተጠቃሚዎች ተናገሩ።

የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በወልድያ ከተማ ስራ መጀመሩ ካላስፈላጊ ወጭ እና ከእንግልት አድኖናል ሲሉ ፓስፖርት ሲቀበሉ ያገኘናቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናግረዋል።

የወልድያ ከተማ የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ፓስፖርት የመስጠት አገልግሎቱን ጀምሯል።

በፓስፖርት ርክክብ መርሃ ግብሩ ላይም የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ እና የአብክመ ማዕድን እና ኢነርጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታምራት ደምሴ ተገኝተዋል።

ፓስፖርታቸውን ሲቀበሉ ካገኘናቸው መካከል ከመርሳ ከተማ የመጣው ራጉኤል አበራ እና ከሀራ ከተማ የመጣው ማህሙድ ማህመድ የኢሚግሬሽን የዜግነት ምዝገባ በወልድያ ከተማ መጀመሩ አገልግሎቱን ለማግኘት ወደሌሎች ከተሞች የምናደርገውን ጉዞ አስቀርቷልናል ሲሉ ተናግረዋል።

ይኼም ካላስፈላጊ እንግልትና ወጭ እንዳዳናቸው ገልጸው አሻራ በሰጠን በአስራምስተኛ ቀን ፓስፖርታችን ተቀብለናል ነው ያሉት።

ሌላኛዋ የወልድያ ከተማ ኗሪ የሆነችው ኢክራም ከዚህ ቀደም አገልግሎቱን ለማግኘት ወደ ሌሎች ከተሞች ይደረግ የነበረውን ጉዞ እና እስከ አራት ወር ድረስ ይሰጥ የነበረውን የቀጠሮ መራዘም እና እንግልት መቅረፍ በመቻሉ ደስተኛ ነኝ ብላለች።

ያለምንም ውጣውረድ አሻራ በሰጠሁ በአስራ አምስተኛ ቀኔ ፓስፖርቴን ተቀብያለሁ ስትልም ተናግራለች።

የቅርንጫፉ አስተባባሪ አቶ ሰይድ ሙሀመድ የቀጠሮ ምዝገባ መስጠት ከተጀመረበት ከየካቲት 16 ጀምሮ 1100 ዜጎችን መመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለውም በተሰጣቸው ቀጠሮ መሠረትም የአምስት መቶ ሃምሳ ሦስት ዜጎች ፓስፖርት ታትሞ እንደመጣ ገልጸዋል።

ማንኛውንም አገልግሎት በጽ/ቤቱ ተገኝቶ መጠቀም እንደሚቻል የገልጹት አስተባባሪው የፓስፖርት ቀጠሮ እንናሰጣለን ከሚሉ አጭበርባሪዎችና ህገወጥ ደላላዎች ማህበረሰቡ እራሱን እንዲጠብቅ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

👉ምንጭ:-የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ነው
መጋቢት 03/2018 ዓ.ም

130ኛዉ የእድዋ የድል በዓል በወልድያ ከተማ በአደባባይ  በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከበረ።የካቲት 23/2018ዓ.ም(ወልድያ ኮሚኒኬሽን)130ኛዉ የአድዋ የድል በዓል በወልድያ ከተማ በአደባ...
02/03/2026

130ኛዉ የእድዋ የድል በዓል በወልድያ ከተማ በአደባባይ በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከበረ።

የካቲት 23/2018ዓ.ም(ወልድያ ኮሚኒኬሽን)

130ኛዉ የአድዋ የድል በዓል በወልድያ ከተማ በአደባባይ በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከብሯል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች በዓሉን በአዳራሽ ከመምከር ባሻጋር በራሳቸዉ ተነሳሽነት የአደባባይ ላይ ትዕይንቶችን ጭምር በማዘጋጀት የድል በዓሉን ዉበት የበለጠ አድምቀዉታል።

አማተር የቲያትር ቡድኖቹም በዓሉን አስመልክቶ የሰርከስ ትርኢቶችን፣ አድዋን አስመልክቶ የተዘጋጁ የግጥም መጣጥፎችን እና የአድዋ የድል በዓልን በአጭሩ የሚያስቃኝ አጭር ተዉኔት አቅርበዋል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ አመለወርቅ ኃይሉ ለበዓሉ ታዳሚዎችም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዕለቱም የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ የተከበሩ አቶ ዱባለ አብራሬ በከተማ አስተዳደሩ እያከናዎኗቸዉ ላለዉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ከወልድያ ከተማ አስተዳደር የስፖርት አሰልጣኞች ማህበር የእዉቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

 በወልዲያ በፍጥነት እየሄደ መሆኑ ተገለጸ።የሶስተኛዉ ዙር የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ለማጠናቀቅ ከታሰበው ባጠረ ጊዜ ለመጨረስ በፍጥነት እየተሰራ ነው ሲሉ የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተ...
20/02/2026


በወልዲያ በፍጥነት እየሄደ መሆኑ ተገለጸ።

የሶስተኛዉ ዙር የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ለማጠናቀቅ ከታሰበው ባጠረ ጊዜ ለመጨረስ በፍጥነት እየተሰራ ነው ሲሉ የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ተናገሩ።

ከንቲባው ይኼን ያሉት ከጎንደር በር _ እቴጌ መዝናኛ እና ከአዳጎ _እቴጌ ጣይቱ ብጡል ትምህርት ቤት ድረስ ባሉ ሳይቶች የሚሰሩ የልማት ስራዎች ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት ነው።

የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ የተለያዩ ስራዎች በሁሉም ሳይቶች በጥሩ ሁኔታ እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው ቦታን ከሦስተኛ ወገን ነጻ የማድረግ ሥራ መቶ ፐርሰንት ተጠናቋል ነው ያሉት።

የስራ እድል መፍጠሪያ የሆኑት የመሸጫ ሱቆች ግንባታ በጥራትና መገንባታቸውን የገልጹት ከንቲባው ሱቆቹ በዚህ ሣምንት ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ርክክብ ይፈጸማል ብለዋል።

ህብረተሰቡ ለልማቱ ተባባሪ በመሆን በተፈለገው ጥራትና ፍጥነት እንዲሰራ ድጋፍ እያደረገ ነው ሲሉም ከንቲባው ተናግረዋል።

ወልድያ በልማቱ እንደ አዲስ ተወልዳ አሸብርቃለች ያሉት የከተማዋ ኗሪ አቶ ባሻ ተፈራ እኔ ሽማግሌው ይኽን ልማት በማየቴ እኔም በደሥታ ታድሻለሁ ብለዋል።

መልካም ነገር ስታይ መልካም ነገር ታስባለህ ያሉት ሌላኛው የከተማዋ ኗሪ አቶ ቢሆነኝ ካሣው ከተማዋ በልማቱ መለወጧን ገልጸው ይኽም ለኗሪዎቿ የመንፈስ እርካታ ሰጥቶናል ነው ያሉት።

በተለያዩ ሳይቶች የሚሰሩ የልማት ስራዎችም በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኙም ኗሪዎቹ ተናግረዋል።

👉መረጃው የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ነው::
የካቲት 13/2018 ዓ.ም

  ላበረከቱ አካላት እውቅናና ሽልማት ሰጠ።የወልድያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በ4ኛ ዙር 13ኛዓመት 40ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ ነው እውቅናና ሽልማት የሰጠው።ምክር ቤቱ በከተማው ውስጥ እየ...
15/02/2026

ላበረከቱ አካላት እውቅናና ሽልማት ሰጠ።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በ4ኛ ዙር 13ኛዓመት 40ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ ነው እውቅናና ሽልማት የሰጠው።

ምክር ቤቱ በከተማው ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን አመስግኖ ለወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ እውቅናና ሽልማት ሰጥቷል።

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ማጠቃለያ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች መካከል ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበው ለወልድያ መሰናዶ ት/ቤት ርዕሰ ላደረገው ጉልህ አስተዋጽኦ እውቅናና ሽልማት ሰጥቷል።

👉መረጃው የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ነው።
የካቲት 07/2018 ዓ.ም

የወልድያ ዩኒቨርስቲ  በዋናው ግቢ ያስገነባውን የህጻናት መዋያ በዛሬው እለት አስመረቀ።ዩኒቨርስቲው በዛሬው እለት ያስመረቀው  የህጻናት መዋያ የተቋሙ ሰራተኞች የብዙ ዘመን ጥያቄ እንደነበር ...
10/02/2026

የወልድያ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ያስገነባውን የህጻናት መዋያ በዛሬው እለት አስመረቀ።

ዩኒቨርስቲው በዛሬው እለት ያስመረቀው የህጻናት መዋያ የተቋሙ ሰራተኞች የብዙ ዘመን ጥያቄ እንደነበር የወልድያ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ.ር አበበ ግርማ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም ልጆች የወልድያን ፣የሰሜን ወሎን ብሎም የወሎን ባህላቸውን እና እሴቶቻቸውን እንዲያውቁ በማድረግ እንደሀገር የሚያስቡ እንደ አለም የሚፈጽሙ ልጆች እናገኝበታለን ብለዋል።

ግንባታውን በተመለከተ በርካታ ልምድ ልውውጥ ወስደን የራሳችን እስታንዳርድ መሠረት በማድረግ በቋሚነት ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆን አቅደን ነው የሰራ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

በቂ ሰራተኞችን አሰልጥነናል ያሉት ፕሬዝዳንቱ ግንባታው በቀጣይ እንደሚስፋፋም ተናግረዋል።


የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ የህጻናት መዋያው ወላጆች በተገቢው መንገድ ሀሳባቸውን ሰብስበው ተግባራቸውን እንዲፈጽሙ እና የመንግስትን የስራ ስዓት እንዲያከብሩ የሚያግዝ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ይህ ፕሮጀክት የቅንጦት አይደለም ያሉት ከንቲባው ለነገ ሀገርን ለመሥራት ዛሬ አስበን የምንሰራው አስፈላጊ ተግባር ነው ብለዋል።

በግድግዳዎቹ ላይ የብርቅዬ እንስሳቶች እና የታዋቂ ሰዎች ምስል፤ ሀገር በቀል የሆኑ የባህላዊ አለባበሶች እና የጨዋታዎች ምስል መካተቱ ህጻናት በተለያዬ መንገድ አካባቢያቸውን እንዲያውቁ የሚያግዝ በመሆኑ የሚበረታታ ነው ብለዋል ።

ነገን የመሥራት ተልዕኳችንን በጋራ ለመወጣት ሌሎች ተቋሞችም በተመሣሣይ መንገድ ሰርተው እንዲጨርሱ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ሲሉ ተናግረዋል።

ዩኒቨርስቲው ከማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት አኳያ የአካባቢውን ችግር ለይቶ ለመደገፍና ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ለመሥራት እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።

የህጻናት መዋያው ከስድስት ወር እስከ አራት አመት ያሉ ህጻናቶችን እንደሚቀበል በቦታው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

👉መረጃው የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ነው
የካቲት 03/2018 ዓ.ም

📚 ለነገው ብርሃን፣ ዛሬ እንተባበር! ✨"እውቀትን ማውረስ፣ ትውልድን መገንባት ነው!"የነገው ትውልድ ብሩህ እንዲሆንና የእውቀት አድማሱ እንዲሰፋ  የመጽሐፍት ማሰባሰብ ንቅናቄ ጀምረናል። ይህ...
04/02/2026

📚 ለነገው ብርሃን፣ ዛሬ እንተባበር! ✨
"እውቀትን ማውረስ፣ ትውልድን መገንባት ነው!"
የነገው ትውልድ ብሩህ እንዲሆንና የእውቀት አድማሱ እንዲሰፋ የመጽሐፍት ማሰባሰብ ንቅናቄ ጀምረናል። ይህ ስራ የጥቂቶች ሳይሆን የሁላችንም ነው፤ ምክንያቱም እውቀት ለሁሉም የሚበራ ችቦ ነውና።
🌟 ይህ ሃሳብ የብዙ ወጣቶች የጋራ ሃሳብ እና በሶሻል ሚዲያም በቁጭት ሲንጸባረቅ የቆየ ፍላጎት ውጤት ነው። አሁን ያንን ቁጭት ወደ ተግባር የምንቀይርበት ጊዜ ላይ እንገኛለን።
🤝 የዚህ በጎ ሃሳብ ደጋፊ የሆናችሁ የሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚዎችና የሃሳቡ ደጋፊዎች በሙሉ፦
እውቀትን ለትውልድ ለማዳረስ በምናደርገው ጉዞ እንድትቀላቀሉን፣
በእጃችሁ ያሉ መጽሐፍትን በማጋራት የብርሃን ምንጭ እንድትሆኑ፣
መልእክቱን በማጋራት (Share) ድምጽ እንድትሆኑን ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የእርስዎ ጥቂት ድጋፍ፣ ለብዙዎች ትልቅ ብርሃን ነው!

.C
​ #ወልድያ

በአመራር ዘመን ለህዝብ ዝቅ ብሎ ማገልገል ግዜ የማይሽረው ታሪክ ነው!ህዝብን ዝቅ ብሎ ማገልገል ምን ያስፈልገዋል ብሎ መለየትና ባፋጣኝ ምላሺ መስጠት በአመራር ዘመን ለህዝብ ዝቅ ብሎ ማገልገ...
30/01/2026

በአመራር ዘመን ለህዝብ ዝቅ ብሎ ማገልገል ግዜ የማይሽረው ታሪክ ነው!

ህዝብን ዝቅ ብሎ ማገልገል ምን ያስፈልገዋል ብሎ መለየትና ባፋጣኝ ምላሺ መስጠት በአመራር ዘመን ለህዝብ ዝቅ ብሎ ማገልገል ግዜ የማይሽረው ታሪክ ነው።

ወልዲያ ከተማ ለረጅም አመት በእርጂናና በብስቁልና እድሜዋን እየገፋች የመጣች ከተማ ነበረች።

ከተማዋ ጥንታዊ ከተማ ከመኾኖም በላይ ላለፉት አመታት የስልጡን ከተማ መገለጫ እሳቤ ነበር ተብሎ የተረዱ በኬንዳና በቆሮቆሮ ኮንቲነር ሸፍነዋት ኑረዋል።

ነገሮችን ስንመለከት ዛሬ ላይ ሁነን መለስ ብለን የጥንቱንና የኾላውን የአሁኑን እና መጪውን ግዜ ለማሰብ ተገደድን።

ወልዲያ ትላንት በብስቁልና ዛሬ ብስቁልናን የተጠየፈች እያበበችና እያማረች የመጣች ዛሬ ላይ ሁነን በዚህ አያያዝ ነገን ወልዲያ ከኢትዮጵያ ምንጥ ከተሞች አንዷ ለአፍሪካ ሞዴል እንደምትኾን ተስፋ ሰንቀናል እንደምትሆንም እርግጠኞች ነን።

ወልዲያ ባለ አራት በር መናገሻ ከተማ ናት ይችን ከተማ የሚያስፈልጋትን አይቶና ተገንዝቦ ለህዝቧቾ ምቹ ከተማ ለማድረግ ደፋ ቀና የሚሉ ጠንካራ የቀኑና ከንቲባ ዱባለ አብራሬን ከመቀመጫችን ተነስተን ለማመስገን ፈለግን።

አቶ የስልጣኔ ባለቤት በተሰማሩበት የስራ መስክ እጂግ ከፍተኛ አቅምና የመፈፀም ብቃት ያላቸው መሪ ናቸው ።

ለከተማዋ ሁለንተናዊ እድገትና ብልፅግና ኢንጅነር፣ መሀንዲስ፣ወታደር፣አመራር፣ ባለሙያ ሁሉንም አማክለው የሚሰሩ ልማት ሲነሳ ወልዲያ ሲነሳ ከንቲባ ዱባለ የእናቶችና አባቶች እንባ አባሺ ድንቅ መሪ ናቸው።

እንዲሁም ከስራቸው ያሉትን ከቀበሌ እስከ ከተማ አስተዳደር ጠቅላላ አመራር እያነቁ፣እየመከሩ መገሰጽ የሚያስፈልገውን እየገሰጹ የተሻለ ልማት እንዲሰራ ቢሮ ከመግባታቸው በፊትም ቢሮ ከወጡ በኋላ እየተሰራ ያለውን ልማት ጎጥ ድረስ ወርደው አስተያየት እየሰጡ እየተከታተሉ ከተማችንን አሁን ከደረሰችበት ያደረሱ በትንሽ ልማት የማይረኩ የከተማችን ድንቅ ከንቲባ በሄደበት ሁሉ ከንቲባ ዱባለ ከንቲባ ዱባለ እየተባለ የሚመሰከርለት ጠንካራ የህዝብ አለኝታ ልጅ ናቸው።

ከንቲባ ወደ መሪነት ከመጡ ማግስት ወልዲያ ከተማ ከምን ወደ ምን የሚለውን ልዩነት ከማውራት የነበረውን እና አሁን ያለውን ብቻ በማየት መፍረድ ይቻላል ።

እኝህ መሪ የስልጡን ከተማን ትልቁን የህዝብ ፍላጎት የተረዱ መሪ ማግኘት መታደል ነው። እሳቸው ወደ አመራር ዘመን የመጡበት ቀን ለወልዲያ ከተማና ነዋሪዎቾ የብርሃን ጮራ የፈነደቀበት እለት ነው።

ከመቀመጫችን ተነስተን እናመሠግንዎታለን🙏። እየሰራችሁት ላለው የከተማችን ጠቅላላ ልማት ከጎንዎ ነን በሀሳብም በጉልበት እናግዛለን እጅግ እናከብረዎታለን ::
ጥር/2018 ዓ-ም

የወልድያ ከተማ የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ3  የከተማ አውቶብሶች ባለቤት ሆነ የርክክብ ስነስረአቱም የተካሄደ ሲሆን ባሶቹ ከነገ ጀምሮ መደበኛ አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን ዛሬ የነጻ ትራንስፖርት...
15/01/2026

የወልድያ ከተማ የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ3 የከተማ አውቶብሶች ባለቤት ሆነ የርክክብ ስነስረአቱም የተካሄደ ሲሆን ባሶቹ ከነገ ጀምሮ መደበኛ አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን ዛሬ የነጻ ትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣሉ ህብረተሰቡም ባሶቹን በሃላፊነት ስሜት እንዲጠቀም መልእክት ተላልፏል!!

ዩኒቨርሲቲው የወልድያ መናኸሪያ ዲዛይንን ሰርቶ አስረከበ ጥር 04/2018 ዓ.ም የወልድያ መናኸሪያ እና ባለ ሰባት ወለል ሁለገብ ህንጻ ዲዛይን በቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይ...
12/01/2026

ዩኒቨርሲቲው የወልድያ መናኸሪያ ዲዛይንን ሰርቶ አስረከበ

ጥር 04/2018 ዓ.ም የወልድያ መናኸሪያ እና ባለ ሰባት ወለል ሁለገብ ህንጻ ዲዛይን በቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በኩል ተሰርቶ ለወልድያ ከተማ አስተዳደርና ሰሜን ወሎ ዞን በዛሬው ዕለት አስረከበ፡፡

አጠቃላይ 6‚099‚508 (ስድስት ሚሊዬን ዘጠና ዘጠኝ ሽህ አምስት መቶ ስምንት ብር) በላይ ወጭን ሊያስወጣ የሚችል ዲዛይን ነው በዩኒቨርሲቲው ተሰርቶ የተሰጣቸው።

ስራን በጋራ ሰርቶ ውጤት እያሳዩ ከሚገኙ ተቋማት መካከል አንዱ የሰሜን ወሎ ዞን ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ጽ/ቤት ማሳያ ነው ያሉት የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምርምር ቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ማርየ በለጠ (ዶ/ር)፤ መናኸሪያ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የሚገለገልበት እንደመሆኑ መጠን አሰራሩን ማዘመንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ዩኒቨርሲቲው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሁኖ በመስራት የበኩሉን ኃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በትራንስፖርት ላይ አትኩሮ መስራት መቻሉ በማህበረሰቡ እንቅስቃሴ ላይ የሚገጥሙ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለማስቀረት ሚናው የጎላ ነው ያሉት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ሲሆኑ የተጀማመሩ ጥሩ ጅምሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከዚህ በላይ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋልም ብለዋል።

ዘመናዊ መናኸሪያ መኖሩና አሰራሩንም ዲጅታላይዝድ ማድረግ ህገወጥ የአሰራር ስርዓቶችን ይቀርፋል ያሉት ከንቲባው፤ የምንረከበውን ዲዛይን በመውሰድ ለመስራት ዝግጅት ማድረግ‎ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ስራውን ለመስራት ያሉ ችግሮችን በጥናት በመለየትና ለችግሮቹም የመፍትሄ ሃሳቦችን በማስቀመጥ ከመንገድ ትራንስፖርቱና መናኸሪያው ጋር ተያይዞ በርካታ ስራዎችንም መስራት መቻሉን የተናገሩት የቴክኖሎጅ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር አማረ ቢሆን ናቸው፡፡ ‎

ከተማዋ ስማርት ሲቲን መሰረት አድርጋ እየሰራች እንደመሆኗ መጠን ዩኒቨርሲቲውም የከተማችንን ውበት ለማስጠበቅ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። በቀጣይም አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

‎የዞኑ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ጽ/ቤት ከዩኒቨርሲቲው ጋር ተቀራርቦ ቢሰራ ውጤታማነቱ የጎላ እንደሚሆን በማመን ዩኒቨርሲቲውም በመናኸሪያ ውስጥ የነበሩ ችግሮችን በጥናት ለይቶ በመሰራቱ የሚታዩ ችግሮች እንዲፈቱ ሁላችንም የየራሳችንን ኃላፊነት ወስደን በመስራታችን በትራንስፖርት ዘርፉ በግልጽ እየታዩ ያሉ ችግሮችን በመቅረፍ የማይታመን ለውጦችን ማምጣት ተችሏል ያሉት ደግሞ የሰሜን ወሎ ‎ዞን ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባንቴ ምስጋናው ናቸው፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች ጀምሮ በርካታ ስራዎችን በመስራቱ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል በማለት ምስጋናቸውን ያቀረቡት ኃላፊው፤ ከተማዋ የስማርት ሲቲን እሳቤን ለማሳካትና ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተረባርቦ የተሰራውን ዲዛይን መሬት ላይ አውርዶ በመስራት የከተማዋን ውበትና የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡን ማሳደግ ይጠበቅብናል ብለዋል።

ዲዛይኑ የተሰራው በቴክኖሎጅ ኢንስቲትዮት የአርክቴክቸር መምህራን መሆኑን የተናገሩት የዲዛይን ስራው ቡድን ሰብሳቢ ስለዲዛይን ገለጻ ያደረጉት መምህር ተስፋለም ካሳዬ ናቸው፡፡
‎የተሰሩትን ዲዛይኖች በዶ/ር ማርየ በለጠ በኩል የወልድያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬና የሰሜን ወሎ ‎ዞን ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባንቴ ምስጋናው ተረክበዋል።
---------------------------

 📸በወልዲያ ከተማ አስተዳደር በቤት ማህበራት የሚገነቡ የአፓርትመንት ዲዛይኖች ቀርበው ውይይት ተካሂዷል።📸በውይይት መድረኩም የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብ...
09/01/2026



📸በወልዲያ ከተማ አስተዳደር በቤት ማህበራት
የሚገነቡ የአፓርትመንት ዲዛይኖች ቀርበው ውይይት ተካሂዷል።

📸በውይይት መድረኩም የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ እና የወልድያ ከተማ አስተዳደር የማህበራት ማስፋፊያ ማደራጂያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ ሲሳይን ጨምሮ የሚመለከታቸው የመምሪያ ኃላፊዎችና የአፓርትማ ማህበራት ስራ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል።

📸በቀረበው የአፓርትማ ዲዛይን ላይ መሻሻል ያለባቸው ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን ዲዛይኑ በቀጣይ የተመላከቱ ነጥቦችን አካቶ እንዲሰራም ሀሳብ ተሰጥቷል።

👉መረጃው:-የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን
ጥር 01/2018 ዓ.ም

"ጥምቀትን በምድረ ገነት/ ወልድያ/ በሚል  መሪ ቃልቀጣዩን የጥምቀት በዓል አከባበር አስመልክቶት ለፈፃሚ አካላት ኦረንቴሽን እና የስራ ተልዕኮ ተሰጠታህሳስ30/2018ዓ.ም(ወልድያ ኮሚኒኬሽን...
08/01/2026

"ጥምቀትን በምድረ ገነት/ ወልድያ/ በሚል መሪ ቃል
ቀጣዩን የጥምቀት በዓል አከባበር አስመልክቶት ለፈፃሚ አካላት ኦረንቴሽን እና የስራ ተልዕኮ ተሰጠ

ታህሳስ30/2018ዓ.ም(ወልድያ ኮሚኒኬሽን)

ቀጣዩን የጥምቀት በዓል አከባበር አስመልክቶ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ወይይት ተካህዷል።

በዓሉ ወልድያ ላይ ልዩ ትርጉም ያለዉና በድምቀት የሚከበር ከመሆኑ አንጻር፤ ከወዲሁ በዓሉን በጥሩ ሁኔታ ማክበር ስለሚቻልበት መንገድ በሰፊዉ ተዳሷል።

በዓሉ በቀጣይ ወልድያ የምታወቅበት እና ገናን ላሊበላ ያከበሩ ቱሪስቶች ጥምቀትን ደግሞ በወልድያ እንዲያከብሩ ለማድረግ ያለመ ስራ መስራት እና ሌላኛዉ መለያችን ሁኖ እንዲቀጥል መሰራት አለበት ያሉት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ናቸዉ።

ከንቲባዉ አያይዘዉም ወልድያ ከላሊበላ ቀጥሎ ሁለተኛዋ የቱሪስት መዳረሻ ከተማ እንድትሆን ከፈለግን ይሄን ተግባር ከፍ አድርገን መፈጸም ከእኛ ይጠበቃል ነው ያሉት።

እንዲሁም ለከተማችን ይሰጥ የነበረዉ ያልተገባ ስምን የምናድስበት እና ለአለም የምናስተዋዉቅበት አንዱ መንገድ መሆኑን አዉቀን የተለየ ትርጉም ሰጥተን ልንሰራዉ የሚገባ ተግባር ነዉ ሲሉ ነዉ የገለጹት።

ሌላዉ ከንቲባዉ የገለጹት በበዓሉ ወቅት የምናከናዉናቸዉ ባህላዊ እና ኃይማኖታዊ ሁነቶች ሰላማዊነታችንን እና እንግዳ ተቀባይነታችንን የሚገልጹ እንጅ ግጭትን እና ሁከትን ሊያስከትሉ የሚችሉ መሆን የለባቸዉም ብለዋል።

ከንቲባዉ በመጨረሻም የበዓሉን አከባበር አስመልክቶ ቅድሚያ መከናዎን የሚገባቸዉን ተግባራት ለባለድርሻ አካላት በየዘርፉ ተልዕኮ በመስጠት አጠናቀዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎችም ተግባራቶቹ ተለይተዉ ለሚመለከተዉ አካል መሰጠቱ ለድጋፍና ክትትል አመች ያደርጋዋል ሲሉ ገልጸዋል።

ታህሳስ 26/04/2018 ዓ.ም ‎የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ወልድያ ቅርንጫፍ በይፋ ስራ መጀመሩን አስታወቀ።‎📸‎አገልግሎቱ በቅርብ መኖሩ ከሚኖረው የጊዜም ሆነ የገንዘብ ወጭ በላይ ህገ...
04/01/2026

ታህሳስ 26/04/2018 ዓ.ም ‎የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ወልድያ ቅርንጫፍ በይፋ ስራ መጀመሩን አስታወቀ።

📸‎አገልግሎቱ በቅርብ መኖሩ ከሚኖረው የጊዜም ሆነ የገንዘብ ወጭ በላይ ህገ-ወጥ ስደትንም እንደሚቀንስ የተናገሩት ም/ፕሬዝዳንቱ ህገ-ወጥ ስደትን በተመለከተ በተደረገው የባለድርሻ አካላት ውይይትና በቀረበው ጥናታዊ ጽሁፍም ለህገ-ወጥ ስደት አንዱና ዋናው ምክንያት አገልግሎቱ በቅርብ አለመኖሩን ተናግረዋል።

📸የኢሜግሬሽንና ዜግነት ጉዳዮች አገልግሎት በዛሬው እለት በይፋ ስራ መጀመሩን ባበሰሩበት መርሀ-ግብር ላይ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ወልድያ ከተማን ጨምሮ የሰሜን ወሎ ዞን ህዝብ ለበርካታ አመታት አገልግሎቱን ለማገኘት ወደተለያዩ ቦታዎች በመሄድ ለከፍተኛ ወጭና እንግልት ሲዳረጉ መቆየቱን ገልጸዋል።

📸‎አገልግሎቱ መጀመር መቻሉ ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው ያሉት ከንቲባው፤ አገልግሎቱ በወልድያ ከተማ እንዲጀመር ላደረጉና ለተባበሩ አካላት ሁሉ ምስጋናቸውንም አቅርበዋል።

📸‎የወልድያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ አቶ ኢቶዮጵስ አያሌው በበኩላቸው ዜጎቻችን በህጋዊ መንገድ ከአንድ ሃገር ወደሌላ ሃገር መጓዝ ሲችሉ ነገር ግን በህገ ወጥ መንገድ በመሄድ ውድ ህይወታቸውንና ገንዘባቸውን ያለምንም ዋጋ እየገበሩ ስለሚገኙ አገለግሎቱ በከተማችን መቋቋሙ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደሚፈልጉት ቦታ ለመሄድምና አገልግሎቱን በቅርብ ማገኘት ያስችላቸዋል ብለዋል።

📸‎አጠቃላይ ስለአገልግሎቱ አላማና አስፈላጊነት
እንዲሁም የወልድያ ቅርንጫፍ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ2019-2021ዓ.ም የኢንቨስትመንት ዕቅድ ለተሳታፊዎች ያቀረቡት የወልድያ ቅርንጫፍ ኃላፊ አቶ ሰይድ መሃመድ ናቸው።

📸‎የሰው ሃይል አቅምን ለማጎልበት፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ አስራርን ለማስፋትና ለሌሎች ዘርፎችም ከወልድያ ዩኒቨርሲቲ ጋር አብረው እንደሚሰሩ የተናገሩት ኃላፊው፤ በቀን 800 በወር 24,000 በዓመት 288,000 ዜጎች በወልድያ ከተማና አካባቢው ያሉ የማህበረሰብ ክፍሎች በቅርንጫፉ አገልግሎቱን ያገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

📸‎የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ወልድያ ቅርንጫፍ በይፋ ስራ መጀመሩን ባበሰረበት በዛሬው ዕለትም የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግና ህገ-ወጥ ስደት ላይ ያተኮረ ፕሮጀክትን ይዞ እየሰራ ያለው የወልድያ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው የስራ ኃላፊዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችም ተገኝተዋል።

Address

Woldia
Woldia

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Telephone

+251949896067

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Sport Club New Page 2013 E.C posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Woldia Sport Club New Page 2013 E.C:

Share