21/02/2026
የጨዋታ ቀን !
ሀዲያ ሆሳዕና 9:00 ባህርዳር ከተማ
የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ውድድር ዛሬ ሲጀምር፣ ክለባችን ሀዲያ ሆሳዕና የካቲት 2 ቀን በተደረገ የ16ኛው ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 በማሸነፍ የመጀመሪያውን ዙር ውድድሩን በድል ማጠናቀቁ ይታወሳል።
ከፋሲሉ ድል በኋላ ቡድናችን አጭር እረፍት አድርጎ ላለፉት ጥቂት ቀናት በሀዋሳ ከተማ ዝግጅት ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ ምንም እንኳን የዝግጅት ጊዜው አጭር ቢሆንም ነብሮቹ ዝግጅታቸውን አጠናቀው ለዛሬው የ20ኛ ሳምንት ፍልሚያ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ሆነዋል።
ዛሬ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ከባህር ዳር ከተማ ጋር በሚደረገው ጨዋታ፣ የመጀመሪያውን ዙር ሽንፈት ለመቀልበስና የደረጃ ሰንጠረዥ ስፍራችንን ይበልጥ ለማሻሻል ወደ ሜዳ የምንገባ በመሆኑ ደጋፊዎቻችን በስታዲየም ተገኝታችሁ እንድታበረታቱን ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ድል ለነብሮቹ ! 💪
⚪️ ⚫️ 🔴