22/11/2025
#ዜና | በ2ኛው የኢትዮጵያ ወጣቶች ኦሎምፒክ ጫዋታዎች ለተሳተፈው የድሬዳዋ ቡድን በተለያዩ መንገዶች አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና ሽልማት ስነስረዓት ተከናወነ ።
| ህዳር 13 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
በድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን አዳራሽ የተከናወነውን የምስጋና ስነስረዓትን ያዘጋጁት የድሬዳዋ ማርሻልአርት ጥምረት መሆናቸው ታውቋል ።
የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ተወካይ አቶ ኃይለማሪያም አማረ በወቅቱ እንደተናገሩት 2ኛው የኢትዮጵያ ወጣቶች ኦሎምፒክ ጫዋታዎች ላይ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኛች እና አሰልጣኞች እንኳን ደሰ ያላቹ ብለው ለወደፊቱም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው መልክታቸውን አሰተላልፈዋል ።
በኢትዮጵያ ማርሻል አርት ስፖርቶች ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው አቶ አይለማሪያም አክለውም በድሬደዋ የማርሻር አርት ጥምረት እንዲመሰረት አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን አመስግነው በድሬዳዋ አስተዳደር በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኘውን የማርሻል አርት ስፖርትን የበለጠ እንዲጠናከር ጥምረቱ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
የቴኳንዶ አሰልጣኝ ሳቦም ተመሰገን ኢላላ በግላቸው ወርቅ ላመጡ ስፖርተኞች የገንዘብ ሽልማት እና ለማርሻል አርት አሰልጣኞች ደግሞ ስጦታ አበርክቶላቸዋል ።
በ2ኛው የኢትዮጵያ ወጣቶች ኦሎምፒክ ጨዋታዎች ድሬዳዋ በማርሻር አርት 3 የወርቅ ሜዳሊያዎችን ማግኘቷ ይታወቃል።
ፍቃዱ ክብረኃይል
ምስል፦እስራኤል ሙሉ
ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦
👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!