Mule Hailu

Mule Hailu i'm responsible to our people

16/05/2026

እሄ ሕዝብ የተደራጀና መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ጦርነት እንደምደረግበት ለማወቅ
❤ ወጣቱ የስራ ዕድል አልፈጠረለትም ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጥሮም እንዳይሰራ መብራት የለም
❤ባንኮች ለንግድ ማሕበረሰቡ ተገቢውን ብድር እንዳይሰጡ ተከልክለዋል
❤በዞኑ ውስጥ የመብራት ሀይል እጥረት እንዲኖር ሆን ተብሎ ተደርጎል። የpower substation ለከምባታ ብርቁ ነው።

14/03/2026

በተደጋጋሚ ተናግረን ሰሚ ያጣንበት ጉዳይ ቢኖር የዞኑ ትልቁ ሳምንታዊ ገበያ መዋያ ቀን ቅዳሜ መሆኑ እየታወቀ ሳምንት እየጠበቁ መብራት ማጥፋት ሕዝቡን ለማስቀጣት ከልሆነ በስተቀር ሌላ ምን ልሆን ይችላል??

20/01/2026

አሁን ባገኘሁት መረጃ ዱራሜ የሚገኘው የማዕከላዊ ኢ/ያ ክልል ግብርና ቢሮ ብቻውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዱራሜ ቅርጫት 62 የአካውንት ቋቶች ያሉት ቢሆንም ባንኩ ለሕዝቡ የሚሆን መሠረተ-ልመት ግን የለውም!

የእኔ አባት አሁን የእግዚአብሔር ምህረት ከአንተ ጋር ይሁን። ሞት እራሱ ሞቷል!
22/12/2025

የእኔ አባት አሁን የእግዚአብሔር ምህረት ከአንተ ጋር ይሁን። ሞት እራሱ ሞቷል!

" ።"እንደምን ሰነበታችሁ የሀገሬ ልጆች? እንደሚታወቀው ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ባለፉት ጥቂት አመታት መደጋገፍና ትብብርን በሀገራችን የተመለከትንበትና የወደቁ የተነሱበት፣ በርካታ የዘመሙ ጎጆዎ...
26/10/2025

" ።"

እንደምን ሰነበታችሁ የሀገሬ ልጆች? እንደሚታወቀው ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ባለፉት ጥቂት አመታት መደጋገፍና ትብብርን በሀገራችን የተመለከትንበትና የወደቁ የተነሱበት፣ በርካታ የዘመሙ ጎጆዎች የተጠገኑበት፣ የሚረዳቸው ጠፍቶ ደዌ ስር ሰዶበቸው በሞት አፋፍ የነበሩ በቅን ልቦች ፍፁም ርህራሄ በተሞላበት ድጋፍና ርብርብ ታክመው የዳኑበት መፅሐፍ ቅዱሳዊ ልምምድን በተግባር ያየንበት ድንቅ ጊዜያቶችን አሳልፈናል።

ዘሬም ወደሚታውቁት የግድግዳዬ ልጥፍ ያመጠኝ አንድ ቅዱስ ዓለማ ነው። ይሃውም የዱራሜ ከተማ ቁ2 ሙሉ ወንጌል ቤ/ያን በኢንዱስትሪያል ኮሌጅ አካባቢ ከ2009 ዓ/ም ጀምሮ የተተከለችና በ2015 ዓ/ም ወደ አጥቢያ ደረጃ ያደገች ከ150 በላይ የተጠመቁ ምዕመንና 90 የሚሆኑ የሰነበት ት/ት የሚማሩ ልጆች ያሏትና የመንግስቱን ወንጌል የምትሰብክ እንዲሁም በፈጣን መንፈሳዊ ዕድገት ላይ የሚትገኝ ቤ/ያን ነች።

ታዲያ የምትገኝበት የመሬት ይዞታ በእጅጉ ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ የልጆች መማሪያ ክፍሎችን፣ የፀሎትና የአገልጋዮች እንዲሁም ለቤ/ያንቱ ቁልፍ አገልግሎቶች የሚያስፈልጉ ግንባታዎችን ለመገንበትና ነበሩን የአምልኮ አደራሽ በጣም የጠበበን በመሆኑ ማስፋት ግድ በሆነብን ሁኔታ ውስጥ እያለን በቤ/ንቱ አጠገብ የሚገኝን በ500 ካሬ ሜትር ላይ ያለን ቤት ለመግዛት ያገኘንና ከሻጩም ጋር ተስማምተን የገንዘብ አቅማችን ያልፈቀደልን በመሆኑ ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦችና ቅን ልብ ያላችሁን ሁሉ ድጋፍ መጠየቅ ግድ ሆኖብናል።

#በመሆኑም መላው ቅዱሳን በቤ/ያንቱ መሪዎች ስም ማለትም አለማየሁ ዴቢሳ፣ መቅደስ ጴጥሮስ እና ከፈለ ማርቆስ ስም በጣምራ በተከፈተው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር #1000723765432 ላይ ልባችሁ ያሳሳበችሁን መንፈሳዊ ድጋፋችሁኝ እንዳታደርጉ በእግዚአብሔር ስም ጥሪ እናቀርብላችኋለን።

#እኔም ለዚሁ የተቀደሰ አላማ ይሆን እግዚአብሔር ከሰጠኝ ላይ #10,000 ብር ገቢ አድርጌያለሁ። ገቢ ያደረግኩበትንም ደረሰኝ አስምጬላችኋለሁ

#ማሳሳቢያ እናንተም ገቢ ያደረጋችሁበትን የባንክ ደረሰኛችሁን በ ወይም 0913358145 Telgram ቁጥሬ ላይ ብትልኩልኝ በቤ/ያንቱና በመላው ቅዱሳን ስም የማስበርካችሁና ምስጋናቸውን በዚሁ ገፄ ላይ የሚገልፅላችሁ መሆኑን ለመግለጽ እወዳለሁ

 !ውድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያን እንዲሁም የቅን ልብ ባለቤቶች የሆናችሁ ሁሉ ከዚህ ቀደም እህታችን ረዲኤት ደምጠው በአጥንት ካንሰር ህመም መታመሟን አስረድታናችሁና ህክምናውንም እን...
28/12/2024

!

ውድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያን እንዲሁም የቅን ልብ ባለቤቶች የሆናችሁ ሁሉ ከዚህ ቀደም እህታችን ረዲኤት ደምጠው በአጥንት ካንሰር ህመም መታመሟን አስረድታናችሁና ህክምናውንም እንድታደርግ የሚያስችል ገንዘብ ለእርሷም ሆነ ለቤተሰቦቿ ባለመኖሩ ከደጋግ ኢትዮጵያውያን 3 ሚሊዮን 8 መቶ ሺህ ብር አሰባስበን ህክምናዋን ለማድረግና ወደ ህንድ ሀገር ማቅናቷን ገልፀንላችሁ እንደነበረ አይዘነጋም።

ነገር ግን ዋናውንና በእግሯ ላይ የነበረውን የካንሰር ዕጢ 10 ሰዓታትን ከፈጀ እልህ አስጨራሽ ቀዶ ጥገና ቦኋላ በስኬት ያጠናቀቀች ሲሆን በተደረገላት ተጫማሪ ምርመራ ካንሳሩ በሰውነቷ ላይ በመሰራጨቱ ምክንያት ከኩላሊቶቿ አንዱን በእጅጉ የጎዳባት በመሆኑ ይህንን የተጎደውን ኩላሊቷን ትታከም ዘንድም ቀደም ስል ከተጠየቀችው ሌላ 1,200,000 /ከአንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ የተጠየቀችና ይህንንም ኩላሊቷን በገንዘብ እጥረት ምክንያት ሳትታከም ወደ ኢትዮጵያ የሚትመለስ ከሆነ የሚጠብቃት ሞት መሆኑን በሐኪሞቹ ተነግሯታል።

ስለሆነም እህታችን ረዲዔት በአሁኑ ሰዓት በመልካም ጤንነት ላይ የሚትገኝ ሲሆን በአስቸኳይ ኩላሊቷ እንዲታከምና ወደ ሙሉ ጤናዋ እንድትመለስ በሀገር ቤትና ከባህር ማዶ የሚትገኙ ወንምና እህቶቿ ድጋፍ እንዲታደርጉላት በፈጣሪ ስም እንለምናችኋለን።

ገንዘብ ገቢ የሚታደርጉላት ውድ የሀገሬ ልጆች እህታችን ረዲኤት ቀደም ስል ትጠቀምበት በነበረው የባንክ አካውንቶች ማለትም

1000162890976 ንግድ ባንክ

5351755991011 dashn bank

013471436377500 awash bank

206408677 abisinya bank በእነዚህ ባንኮች ገቢ ልታደርጉላት የምትችሉ መሆን ልገልፅላችሁ እወዳለሁ

 !ውድ ወንድማችን   የሚኖረው በአሜሪካ ሀገር ቺካጎ ከተማ ነው። ከሰሞኑ የውድ እህቱ ረዲዔት ደምጠው ህመም አሞት ቆይቷል። ዛሬ ደግሞ ህንድ ሀገር ሄዳ ህክምናውን እንዳታደርግ 30,000 ሽ...
13/11/2024

!
ውድ ወንድማችን የሚኖረው በአሜሪካ ሀገር ቺካጎ ከተማ ነው። ከሰሞኑ የውድ እህቱ ረዲዔት ደምጠው ህመም አሞት ቆይቷል። ዛሬ ደግሞ ህንድ ሀገር ሄዳ ህክምናውን እንዳታደርግ 30,000 ሽህ ብር ልኮላታል።
ወንድሜ ስለአንተና ቤተሰብህ እግዚአብሔር ይመስገን ክፉ አይንካህ ዘመንህ ይለምልም።

 🙏 ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቷት እህታችን   የምትባል ስትሆን ትውልዷና እድገቷ  በከምባታ ዞን መዲና በሆነችው በዱራሜ ከተማ ነዉእህታችን ረድዔት በ10 ቀን 2013 ዓ.ም ድንገት የሞተ...
27/10/2024

🙏

ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቷት እህታችን የምትባል ስትሆን ትውልዷና እድገቷ በከምባታ ዞን መዲና በሆነችው በዱራሜ ከተማ ነዉ

እህታችን ረድዔት በ10 ቀን 2013 ዓ.ም ድንገት የሞተር ሳይክል አደጋ በግራ እግሯ ደርሶባት በዱራሜ ዶ/ቦጋለች ገብሬ አጠቃለይ ሆስፒታል ስትታከም ቆይታ : ጨርሶ ሊሻላት ባለመቻሉ : ሻሸመኔ ፈያ ሆስፒታል ፣ ወላይታ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል፣ በ ሀዋሳ ያኔት ሆስፒታል ፣ በሀዋሳ ፓነስያ ሆስፒታል እና ጥቁር ዓንበሳ ሆስፒታል ተዟዙራ የታከመች ሲሆን በወቅቱ በአንፃራዊነት የተሻላት መስሎ ወደ ቤቷ ብትመለስም እያደር ሕመሟ እየባሰና ጉዳት የደረሰባት እግሯ ላይ የተለየ እድገት በመታየቱ በድጋሚ ወደ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታልና ወደ ጥቁር አንበሳ ሪፈር ተደርጋ ለወራት ሕክምና ብትከታተልም ጉዳዩ ከታሰበውና ከተገመተው በላይ ሆኖ ተገኝቷል።

በአደጋው የተጎዳው እግሯም በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ የተለያዩ ስፔሻሊስት ዶክተሮች ያሳወቁ ሲሆን በመጨረሻም የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአጥንት ቀዶ ህክምና ክፍል ዋና ዳይሬክተር #ፕ/ር_ብሩክ_ላምብሶ የወጣቷ ረድዔት ህክምና በሀገር ውስጥ የማይቻል እንደሆነና ሕይወቷን ለመታደግ በአፋጣኝ ወደ ሕንድ ሐገር ሄዳ መታከም እንዳለባት ሪፈር የፃፉ ሲሆን
ለህክምናና መሰል ወጪዎች የተጠየቀው 3,800,000 ብር ነዉ።

እጅግ የተወደዳችሁ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን የዚህችን ባለ ተስፋ ወጣትን ሕይወት ለመታደግ ፈጣሪ ከሰጣችሁ ላይ ልባችሁ የፈቀደውን በመስጠት የእህታችንን ረድዔት ዳምጠውን የደበዘዘ ተስፋ ዳግም በማለምለም የቆዘመውንም ቤተሰብ ከሐዘን በማስወጣት ኢትዮጵያዊ መልካምነታችሁን እንድትገልፁልን በልዑል እግዚአብሔር ስም እንማፀናለን 🙏



commercial bank 1000654819436

Awash bank 013471436377500

Dashin bank 5351755991011

Birhan bank 1030982950414

Abisinya bank 206408677

ለበለጠ መረጃ:-

#0931365246 ወ/ሮ ፍቅሬ ሻሜቦ (እናቷ)
#0916276346 አቶ ዳምጠው ላንገና (አባቷ)

በማድረግ ለቅን ልቦች መረጃውን ማዳረስ አንዱ የእርዳታ አካል ነውና መረጃውን ለወዳጅ ዘመድ በማድረግ ያጋሩልን🙏

በዚሁ አጋጣሚ ደጋግ ልብ ያላችሁ በውጭ ሀገራትና በሀገር ቤት የምትገኙ ሁሉ በተገለፁት የባንክ አካውንቶች ብቻ በመጠቀም ገንዘብ ገቢ እያደረጋችሁ የባንክ ስልፖቻችሁንና ስክሪን ሸት ብትልኩልኝ በደጋግ ልቦችና በረድዔት ስም በfb ገፄ ላይ በቅደም ተከተል ምስጋናችንን የምናቀርብላችሁ ይሆናል።

ጌጡ ተመስገን እንደፃፈው!🇿🇦  የእውቅነና ሽልማት ፕሮግራም !!   | የሚሰሩ ታታሪና ሞዴል ወጣቶችን መሸላምና መመስግን የቀጣይ ትውልድ የቤት ሥራ መሆን አለበትብዙ ጊዜ ለአንድ አከበቢና ማ...
28/05/2024

ጌጡ ተመስገን እንደፃፈው!
🇿🇦 የእውቅነና ሽልማት ፕሮግራም !!

| የሚሰሩ ታታሪና ሞዴል ወጣቶችን መሸላምና መመስግን የቀጣይ ትውልድ የቤት ሥራ መሆን አለበት

ብዙ ጊዜ ለአንድ አከበቢና ማህበረሰብ ወይም ለሀገር የሚለፉ፤ ለነፃነት የሚታገሉ ፤ አንድነትን የሚሰብኩ፤ ጭቆና የሚጠሉ ሰዎችን ማመስገን አለመድንም። ምክንያቱም አንድ ማህበረሰብ ጥሩ የሰራውን ጥሩ ፤ ጀግናን ጀግና ማለት ውርደት ይመስልናል ፡፡

ስለዚህም ትግል እንዴት እንደሆነ ? ... ችግር ምን እንደሆነ ?... ሰላም ማጣት ምን እንደሆነ? ... ሞት ምን እንደሆነ? ... ውስጥ ገብተን ካላያን ሁሉም ሰምም ይመስልናል። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር በታች እግዚአብሔር ራዕይን ፤ እውቀትን ፤ ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ የሚታገሉ ሰዎችን ይሰጠናል ፡፡

ስለዚህ እኛ ደግሞ ጀግናን ጀግና ጎበዝን ጎበዝ በርታ ከጎን ነን ማሌት ባህላችን እናድርግ ፣የሚታገሉ ወጣቶችን መክበር ፤መሸለም ሌል ሀገርን፤ ሕዝብን፤ ማንነትን የምወድ ዜጋ መፍጠር ነው ፡፡ ሆኖም ግን የአንድን ሰው እውቅና መስረቅ ሀገርን ማፍረስ ነው፣ተተኪውን ትውልድ እንዳይሰራ ማደናቀፍም ጭምር ነው። ገዛኸኝ ስራዎቹ ምስክር ናቸው። በደቡብ አፍሪካ ለስራቸው ስራዎች በዞንም በፌደራል ደረጃ ሊደረግለት የሚገባውን ሁሉ የሚመለከተው አካል እንዲያደርግም በአፅንኦት ብለዋል።

'የሀገር ባለውለታን ማመስገን የነገን ትውልድ መቅረፅ ነው'' _ የከምባታ ዞን ተወላጆች በደቡብ አፍሪካ በብሉቃኔና አካባቢዋ የሚኖሩ የከምባታ ዞን ተወላጆች በደቡብ አፍሪካ
በበቃ ዘመቻ እና የተሳካለት ኢትዮጵያዊ በማለት ላለፉት በርካታ አመታት በሀገር ገፅታ ግንባታ ላይ ለሰራው ስራ የምስገና እና እውቅና ፕሮግራም አካሄዶል ፡፡

ላለፉት በርካታ አመታት በሀገር ገፅታ ግንባታ ላይ ለሰራው በደቡብ አፍሪካ የናሽናል ኢንፎርማልና የኢፒኤፍና የሰብስ ኮምኒቲ አባል ለሆናው ለአገልጋይ ገዛኸኝ ሱማሞ የእውቅና ፕሮግራም አዘጋጅተዋል።

በዚህ እውቅና ፕሮግራም ላይ ስለሀገር ልማት ስለሰው ልጆች መብት ላለፉት አመታት ለሰራው መልካም ስራዎች በስፍራው የሀገር ሽማግሌዎች የአካባቢው ታታሪ ሰራተኞችና ከማህበረሰብ ጋር በጋራ ደማቅ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።

ብሎም ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሲመሰረት በሀብት ክፍፍል ላይ በከምባታ ጠምባሮ ላይ በደረሰው በደል ይህ አይገባም በማለት ፍትህን ፍለጋ ብዙዎችን በማስከተል በአንድ ድምፅ ወደ ማንዴላ አደባባይ የወጣ ፍህሓዊም ሰው ነው።

ለነገ ትውልድ ድልድይ እየገነባ ያለና በከምባታነት ላይ ብሎም በኢትዮጵያዊነት ላይ የሰራና እየሰራ ያለ በመሆኑ ለዚህ ብርቱ ወጣት የምስጋና ፕሮግራም አዘጋጅተናል።

እኛ ይህንን ፕርግራም ስናዘጋጅ ለሀገራቸው የሚሰሩ ሰዎችን በርቱ ለማለት ነውና በርቱ ስንልና ስናበረታታቸው ደግሞ የተሻለ ብርቱ ትውልድ እንደሚፈጠር በማሰብ ጭምር ነው።

በብሉቃኔ አካባቢ የምንኖር የዞኑ ተወላጆች ይህ ወጣት ገና በወጣትነቱ ለኢትዮጵያ ላበረከተው በጎ ስራዎቹ ከዚህ በላይም ሊደረግለት ይገባል ስንል ስራዎቹ ምስክር በመሆናቸው ጭምር ነው፡፡

በደቡብ አፍሪካ የወንድሞቻችን ሞት መቀነስ፤ ጭቆና ህጋ ወጥ ስደት መቀነስ የዚህ ወጣት ውጤትም ጭምር ነው።

ወገኖቻችንን ማበርታታት ባህላችን ይሁንም ብላዋል፣ በተለይም የሀገራችንን ለውጥ ለመደገፍ ለህዳሴ ግድብ ሱቅ ለሱቅ ኩፖኖችን በመሸጥ እናም ኢትዮጵያ በምዕራባውያን በተከበበች ጊዜ የተለያዩ ተቋማትን በማስተባበር የአምበሳውን ድርሻ ስለተወጣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ይገባዋል የምንለው ያለምክንያት አይደለም። ስለዚህ የለፋውን በርታ ካላልን ትውልድን አናተርፍም።

በብሉቃኔና አካባቢው የምንኖር የዞኑ ተወላጆችና ወዳጆች በዞናችን እየታየ ያለውን የልማት እንቅስቃሴ አጥብቀን የምንደግፍ መሆኑን እንገልፃሌን ፡፡

በትውልድ መሃል ለትውልድ የሚሰረ ፤የሚጨናቅና ለትውልድ ነፃነት የሚታገሉ ወጣቶችን መክበር ፤መሸለም ሌል ሀገርን፤ ሕዝብን፤ ማንነትን የምወድ ዜጋ መፍጠር ነው ፡፡

የሀገር ፍቅርን የሚገልፁ ወጣቶችን ማበረታታት ባህላችን ዋነኛ ምሰሶ እንዲሆን ጭምር በመሆኑ ውድ ኢትዮጵያውያን ፤በመዕከለዊ ኢትዮጵያ ክልል የከምባታ ፤ሀድያ ጠምባሮ ወለይታ መለው የኢትዮጵያ ህዝብ በስደት ሃገር የለችሁ የዝህን ጀግና ወጣት ጥንካሬ በገኛቹት አግጣም እንድተማሰግኑ ጥሪ ለማቅረብ እኖዳለን።

ለህዝባችን የለፋውን ወጣት እኛም በዚህ መልኩ በርታልን በማለት የምስጋና ፕሮግራም በደቡብ አፍሪካ በብሉቃኔ ፕሮቨንስ የምንገኝ የዞኑ ተወላጆችና ወዳጆች ይህንን ለማዘጋጀት በቅተናል።

በፕሮግራሙም የከምባታ የልማት ቴሌቪዥን ዝግጅት ክፍል የኢሜጅ ኦፍ አፍሪካ ዩዝ ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን የአፍሪካ ገፅታ የወጣቶች ልማት ድርጅት የጋራ ተግዳሮቶችና የገፅታ ግንባታ የሲ.ፒ.ኤ.ፍ ና ሰብስ አባል በመሆን ናሽናል ኢንፎርመር በመሆን በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሱ የጋራ ተግዳሮቶችን እየሰራ ያለ ሲሆን በቀጣይም በዚሁ መርሐ ግብር ወጣቶችን በመመልመልና ተተኪን በማሰልጠን ተተኪን ለማፍራት እየሰራ እንደሆነ የቀኑ ክቡር እንግዳና
በደቡብ አፍሪካ የናሽናል ኢንፎርማልና የኢፒኤፍና የሰብስ ኮምኒቲ አባል አገልጋይ ገዛኸኝ ሱማሞ ተነግራዋል ፡፡

በመጨረሻም የቀኑን እንግዳ ጀግነውን የኢሜጅ ኦፍ አፍሪካ ዩዝ ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን የአፍሪካ ገፅታ የወጣቶች ልማት ድርጅት የጋራ ተግዳሮቶችና የገፅታ ግንባታ የሲ.ፒ.ኤ.ፍ ና ሰብስ አባል በመሆን ናሽናል ኢንፎርመር በመሆን በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሱ የጋራ ተግዳሮቶችን እየሰራ ያለ የኢፒኤፍና የሰብስ ኮምኒቲ አባል አገልጋይ ገዛኸኝ ሱማሞ ስጦታና ምርቃት ለቀጠይ ትልቅ አደርና ሀለፍነት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠነቋል ፡፡

አዘጋጅ ኮሚቴ እና የብሉቃኔና አካባቢዋ የሀገር ሽማግሌዎች🛍️🎁

✍️✍️✍️

ወንድማችሁ አገልጋይ ገዛኸኝ ሱማሞ
#አመሰግናለሁ🙏🏽

ወንድማችን ፍቅሩ አየለ ሳይታከም እረፍት የለንም ብለዋል ሁሉም የዱራሜ ከተማ ወጣቶች።  የኦሮሚያ ኮኦፕሬቲቪ ባንክ ማናጀር ፀጋዓብ ወልዴ 1000 ብር እጅ በእጅ ገቢ አድርጎልናል።ፀግሽ ወንድ...
19/05/2024

ወንድማችን ፍቅሩ አየለ ሳይታከም እረፍት የለንም ብለዋል ሁሉም የዱራሜ ከተማ ወጣቶች። የኦሮሚያ ኮኦፕሬቲቪ ባንክ ማናጀር ፀጋዓብ ወልዴ 1000 ብር እጅ በእጅ ገቢ አድርጎልናል።

ፀግሽ ወንድሜ የያዝከው የጨበጥከው ሁሉ ይባረክልህ።

ለወንድማችን ፍቅሩ አየለ የልብ ቀዶ ህክምና ወጣቶች የሚያደርጉት ርብርብ ቀጥሏል። ወጣት ዳግም (ቹቹ)  ማርቆስ ለወንድማችን ህክምና 2000 ሺህ ብር ገቢ አድርጎልናል።ቹችዬ ስለደረግከው መል...
19/05/2024

ለወንድማችን ፍቅሩ አየለ የልብ ቀዶ ህክምና ወጣቶች የሚያደርጉት ርብርብ ቀጥሏል። ወጣት ዳግም (ቹቹ) ማርቆስ ለወንድማችን ህክምና 2000 ሺህ ብር ገቢ አድርጎልናል።

ቹችዬ ስለደረግከው መልካምነት እግዚአብሔር አምላክ ብድራቱን ይክፈልህ።

Address

Durame

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mule Hailu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category