Hambaricho Durame -ሀምበሪቾ ዱራሜ

Hambaricho Durame -ሀምበሪቾ ዱራሜ The Official Page

የማይቀርበት ታላቅ ዝግጅት የፊታችን እሁድ በዱራሜ ጠላቶቹን እርር፣ ጭርጭር፣ ቅጥል የሚያደርገው አርሴናል!✌ ለመድፈኛው ቤተሰቦች እንኳን ደስ አለን!አርሰናል ለ22 ዓመታት ከተጠማበት የፕሪም...
21/05/2026

የማይቀርበት ታላቅ ዝግጅት የፊታችን እሁድ በዱራሜ

ጠላቶቹን እርር፣ ጭርጭር፣ ቅጥል የሚያደርገው አርሴናል!✌ ለመድፈኛው ቤተሰቦች እንኳን ደስ አለን!

አርሰናል ለ22 ዓመታት ከተጠማበት የፕሪምየር ሊግ ዋንጫ ጋር የተገናኘበት ታሪካዊ ቀን፣ ለመድፈኞች በደስታ፣ በስኬት እና በድል አድራጊነት የተሞላ እጅግ ታላቅ የክለቡ የደስታ ቀን ነው።

የዋንጫው ታሪክ፡ የክለቡ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እና ተጫዋቾቹ ለረጅም ዓመታት ያሳዩት ትጋት ፍሬ አፍርቶ ክለቡን ከከፍተኛው የሊጉ ደረጃ ላይ አድርሰዋቸዋል።

የደጋፊዎች ስሜት፡ ለአመታት ለደረሰው መከፋትና ትዕግስት ምላሽ የሆነው ይህ ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደጋፊዎች በታላቅ ድምቀት የሚያከብሩት የድል አመት ሆኗል።

የአሸናፊነት ጉዞ፡ ቡድኑ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ አልፎ የአውሮፓና የእንግሊዝ እግር ኳስን በበላይነት ለመምራት የሚያስችለውን ብቃት እንዳሳየ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው።

ሀይሌ አለሙ ከዱራሜ
sport ++

21/05/2026

በፈጣን ዜና አቀራረቡ የሚታወቀው ቲክቶከር ዲላን ፔጅ ወደ ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ መጥቷል!!

በፈጣን ዜና አቀራረቡ የሚታወቀው እና ከ19 ሚሊዮን በላይ የቲክቶክ ተከታዮችን ማፍራት የቻለው ዝነኛው የይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ (Dylan Page) ከኢትዮጵያዊው ቲክቶከር አዶናይ ጋር አዲስ አበባ ገብቷል።

ዲላን ወደ ኢትዮጵያ በአካል ሲመጣ የመጀመሪያው ሲሆን ኢትዮጵያ በመምጣቱ ደስተኛ መሆኑን እና የአዲስ አበባ ውበት እንዳስደመመው ገልጿል።

ሆቴል ጀምራችው ያላጠናቀቃችው በቶሎ ገንብታችው አጠናቅቁ ባታጠናቅቁ እግዚአብሔር ሌሎችን እያስነሳ እቺን ከተማ ይለውጣል" ፦ ክቡር አቶ አረጋ እሼቱ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በሆቴል ምር...
02/05/2026

ሆቴል ጀምራችው ያላጠናቀቃችው በቶሎ ገንብታችው አጠናቅቁ ባታጠናቅቁ እግዚአብሔር ሌሎችን እያስነሳ እቺን ከተማ ይለውጣል" ፦ ክቡር አቶ አረጋ እሼቱ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በሆቴል ምርቃቱ ዕለት ያስተላለፉት መልዕክት

በዛሬው ዕለት በሆቴል ዘርፍ ውስጥ ጀምሮ የመጨረስ ፣ አቅዶ የማሳካት ተምሳሌት የሆነው ኬብሮን ኢንተርናሽናል ሆቴል እየተመረቀ ይገኛል።

በዱራሜ ከተማ በአቶ ተመስገን ታደሰ እና ቤተሰቦቹ በ170 ሚሊየን ብር ውጪ የተገነባው የኬብሮን ኢንተርናሽናል ሆቴል!

ኬብሮን ኢንተርናሽናል ሆቴል በውስጡ የእንግዳ ማረፊያ ፣ የካፌና ሬስቶራንት፣ ከ500 በላይ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል የስብሰባ አዳራሾችና ሌሎችንም አገልግሎቶች ያካተተ የዱራሜ ከተማን ብሎም የዞኑን የሆቴል ቱሪዝም አንድ ደረጃ ከፍ ያደረገ ሆቴል ነው።

Misiker Beratu Anshebo

ሞተር ሰርቀው የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!‎ከከምባታ ዞን ዱራሜ ከተማ አፓቼ (Apache) ሞተር ሰርቀው የነበሩ ተጠርጣሪዎች በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ውስጥ በፖሊስ እጅ ከፍንጅ ተይዘ...
26/04/2026

ሞተር ሰርቀው የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!

‎ከከምባታ ዞን ዱራሜ ከተማ አፓቼ (Apache) ሞተር ሰርቀው የነበሩ ተጠርጣሪዎች በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ውስጥ በፖሊስ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

ወንጀሉ የተፈፀመው በዱራሜ ከተማ ሲሆን አንደኛ ተጠርጣሪ ተከተል ኤሊያስ የዱራሜ ከተማ ነዋሪ ሁለተኛው ተጠርጣሪ አቶ ኤፍሬም ሳሙኤል ወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ ነዋሪ የሆነ በዱራሜ ከተማ በዘራሮ ከተማ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቀይ መስቀል ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ነዋሪ የሆኑት አቶ ብሩክ አዴሎ የተባሉ ግለሰብ ቤትን ዕለተ ዕሮብ ሚያዚያ 15 2018 ዓ/ም በግምት ከሌሊቱ 9 ሰዓት አከባቢ ሰብረው በመግባት አፓቼ /Apache/ ሞተር ሰርቀው ከአከባቢው በመሰወር በቀን 16/08/2018 ከሌሊቱ 6:00 አከባቢ ወደ ሮጲ መስመር ይዘው እያሄዱ እያለ በሀለባ ቁሊቶ ከተማ ውስጥ በሚያልፉበት ሰዓት በሁኔታቸው የተጠራጠረው የሀላባ ፖሊስ አባል በድብቅ ስከታተላቸው ቆይቶ ፍቅረ ሰላም ሆቴል ለመሸሸግ ሲገቡ የሀላባ ፖሊስ አባላት ደርሰው ተጠርጣርዎቹን ከሰረቁት ሞተር ጋር በነበሩበት እጅ ከፍንጅ ልይዙ ችለዋል። ያመለጡ ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው እየተፈለጉ ይገኛሉ።

‎ ወንጀልን በጋራ እንከላከል !!

እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል!!የከምባታ ዞን ትራፊክ ፖሊስ አባላት ከታሪፍ በላይ አላግባብ ሲያስከፍሉ የነበሩ መኪናዎችን ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ በቅንጅት ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።Go...
24/04/2026

እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል!!

የከምባታ ዞን ትራፊክ ፖሊስ አባላት ከታሪፍ በላይ አላግባብ ሲያስከፍሉ የነበሩ መኪናዎችን ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ በቅንጅት ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።

Good Job 🙏

እርምጃውን እንዴት ተመለከታችውት?

  ።‼️የ33ኛ ሳምንት ተጠባቂ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ✍️ በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነገ [እሁድ] ምሽት 12:30 ላይ በእንግሊዙ ማንቸስተር ከተማ ኢትሃድ ስታዲየም ማ...
18/04/2026



‼️የ33ኛ ሳምንት ተጠባቂ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ

✍️ በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነገ [እሁድ] ምሽት 12:30 ላይ በእንግሊዙ ማንቸስተር ከተማ ኢትሃድ ስታዲየም ማንቸስተር ሲቲ አርሰናልን ያስተናግዳል።

✍️ አርሰናል በ70 ነጥቦች ሊጉን እየመራ ቢሆንም ከመቸውም በላይ ይህን ጨዋታ ማሸነፍ ወሳኝ 3 ነጥቦችን እንዲያሳካ እና ሚኬል አርቴታ አንድ እጁን ወደ ዋንጫው እንዲያስጠጋ ያደርጋል።

✍️ጥሩ አቋም ላይ ያለው ማንቸስተር ሲቲ አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው በ64 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ማንቸስተር ሲቲ አርሰናልን አሸንፎ የቀረውንም ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ከአርሰናል ጋር እኩል አድርጎ በግብ ልዩነት ብቻ የሚበላለጡ ይሆናል።

ይህ እንደ ፍፃሜ እየተጠበቀ ያለውን ጨዋታ ማን የሚያሸንፍ ይመስላችኋል?

[ማንቸስተር ሲቲ ወይስ አርሰናል?]

✍ይህን ጨዋታ ባማረ እና ወብ በሆነ መልኩ ለእናንተ ለቤተሰቦቻችን ልናሳያችሁ ዝግጅታችንን አጠናቀን የእናንተ መምጣት ብቻ እንጠብቃለን

መላው የሀላባ ህዝብ እንኳን ደስ አላችው! ሀላባ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አደገ ሀላባ ከተማ ወደ 2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ።በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2018...
15/04/2026

መላው የሀላባ ህዝብ እንኳን ደስ አላችው! ሀላባ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አደገ

ሀላባ ከተማ ወደ 2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ።

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2018 የውድድር ዘመን ምድብ "ለ" 20ኛ ሳምንት ጨዋታ ዛሬ በሀላባ ከተማ እና ደሴ ከተማ መካከል ሀዋሳ ላይ ተደርጓል።

በዚህም ጨዋታ ሀላባ ከተማ ደሴ ከተማን 1 ለ 0 በማሸነፍ ነጥቡን 38 አድርሶ አንድ ጨዋታ እየቀረው በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል።

የሀምበሪቾ ገፅ እና ቤተሰቦች ወንድም የሀላባ ህዝብ ወደ ተወዳጁ የኢትዮጵያ ኘሪምየር ሊግ በማደጉ የተሰማውን ደስታ መግለፅ ይወዳል። እንኳን ደስ አላችው!!

የኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ ሰብሮ ሥርዓተ ቀብር በዱራሜ ከተማ በክብር ተፈጸመ።ላለፉት 21 ዓመታት በፖሊስነት ሙያ አገራቸውንና ሕዝባቸውን በታማኝነትና በቁርጠኝነት ያገለገሉት የኮማንደር አልማ...
15/04/2026

የኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ ሰብሮ ሥርዓተ ቀብር በዱራሜ ከተማ በክብር ተፈጸመ።

ላለፉት 21 ዓመታት በፖሊስነት ሙያ አገራቸውንና ሕዝባቸውን በታማኝነትና በቁርጠኝነት ያገለገሉት የኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ ሰብሮ ሥርዓተ ቀብር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ፣ የሥራ ባልደረቦቻቸው፣ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በዱራሜ ከተማ በክብር ተፈጸመ።

ኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ በከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ በተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች ላይ የቆዩ ሲሆን፣ የመምሪያው የማኔጅመንት አባል በመሆንም እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ድረስ መንግሥትንና ሕዝብን በጽናት አገልግለዋል።

በከፍተኛ የፖሊስ አመራርነት ዘመናቸውም መልካም ሥነ-ምግባርን የተላበሱ፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸውና ለአባላት አርዓያ የሆኑ እንዲሁም በርካታ ብቁ የፖሊስ አባላትን ያፈሩ ብርቱና ተምሳሌት መኮንን ነበሩ።

ከሙያዊ ግዴታቸው ባሻገር፣ በተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ በግንባር ቀደምትነት በመሳተፍና ኅብረተሰቡን በማስተባበር የተቸገሩ ወገኖችን ሲረዱ የቆዩ ደግ እናት ነበሩ።

ኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን በኩል ለስትራቴጂክ አመራር ስልጠና የቀረበውን መስፈርት በብቃት አልፈው፣ በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ "ዋር ኮሌጅ" (War College) ከፍተኛ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ነበሩ።

የትንሳኤ በዓልን ከቤተሰቦቻቸው ጋር አክብረው ወደ ትምህርት ገበታቸው አዲስ አበባ በመመለስ ላይ እንዳሉ፣ ሚያዚያ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:35 ላይ በታጠቁ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።

የሁለት ሴትና የአንድ ወንድ ልጅ እናት የነበሩት የኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ ሕይወት ማለፍ፣ ለመላው የጸጥታ መዋቅርና ለከምባታ ሕዝብ ትልቅ ሐዘን ሆኗል።

በሥርዓተ ቀብሩ ላይ የተገኙት የሥራ ባልደረቦቻቸውና ወዳጆቻቸው፣ ኮማንደሯ ለሙያቸው የነበራቸውን ፍቅርና ለሕዝብ የከፈሉትን መሥዋዕትነት በታላቅ አክብሮት ዘክረዋል።

የጀግናዋ ኮማንደር ነፍስ በሰላም ትረፍ፤ ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።

በቀብር ሥነሥርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ ፣የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ ፣ የከምባታ ዞን ፖሊስ አዛዥ ረ/ኮሚሽነር ታገሰ አርፍጮን ጨምሮ ከፍተኛ የክልሉ እና የዞን የሥራ ኃላፊዎች ፣ የሥራ ባልደረቦቻቸው ፣ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።

Address

Durame
Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hambaricho Durame -ሀምበሪቾ ዱራሜ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hambaricho Durame -ሀምበሪቾ ዱራሜ:

Shortcuts

Share