12/05/2026
የዓለም አትሌቲክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጆን ረጂዮን አዲስ አበባ ገቡ
የዓለም አትሌቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጆን ረጂዮን እና የጨረታዎች፣ ውድድሮች እና ሁነቶች ዳይሬክተ ማርክ ሀስት ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ቦሌ ዓለምአቀፍ አየር ማረፊያ በመገኘት ደማቅ አቀባበል አድርገዉላቸዋል።
የዓለም አትሌቲክስ ከፍተኛ አመራሮች ኢትዮጵያ መምጣት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከዓለም አትሌቲክስ ጋር የጀመረውን የስፖርት ዲፕሎማሲ የበለጠ የሚያጠናክር ይሆናል።
አመራሮቹ በመገባደድ ላይ የሚገኘውን የ አደይ አበባ ዓለምአቀፍ ስቴዲየምን ጨምሮ ሌሎች የአትሌቲክስ መሰረተ ልማቶች ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ በቀጣይ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናን ጨምሮ 2028 አልቲሜት ሻምፒዮን ሺፕ ለማዘጋጀት ለዓለም አትሌቲክስ ጥሪ ማቅረቧን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል።
( AMN )
ግንቦት 4/2018 ዓ.ም