27/07/2026
ድሬዳዋን በመወከል የተወዳደሩት አቶ ቢኒያም ነገሱ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ሆነው ተመረጡ!
አቶ ቢኒያም በትምህርት ፣ በሙያ፣ በቴክኖሎጂ እና በስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ አሻራ ያሳረፉ ሲሆን፣ በተለይም የብስክሌት ስፖርትን ከታች ጀምሮ ለማሳደግ፣ ታዳጊዎችን ለማብቃት ፣ ውድድሮችን ለማዘጋጀት እና ዘርፉን በዲጂታል መረጃ ለማገልገል ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው።
“ዘመናዊ አሰራር ፥ ጥራት ያላቸውን ክለቦች ማዘመን ፥ በሀገራችን ብስክሌት ውስጥ ለውጥ ማምጣት እና የውጤት ታሪክ መገንባት ራዕያችን ነው!" ያሉት አቶ ቢኒያም የኢትዮጵያን የብስክሌት ደረጃ አሁን ካለበት ከፍ የማድረግ ዕቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።
መልካም የስራ ዘመን እኒዲሆንላቸው ተመኘን!