ይርጋጨፌ ቡና ስፖርት ክለብ

ይርጋጨፌ ቡና ስፖርት ክለብ ይህ የይርጋጨፌ ቡና ስፖርት ክለብ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ነው

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንትየቤላ ስፖርት የጨዋታ ኮከብ የኔነሽ አበበ
16/05/2026

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት

የቤላ ስፖርት የጨዋታ ኮከብ

የኔነሽ አበበ

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት ⌚️ ሸገር ከተማ 0-0 ይርጋጨፌ ቡና
16/05/2026

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት

⌚️

ሸገር ከተማ 0-0 ይርጋጨፌ ቡና

" ለመጣው ውጤት እውቅና በመስጠት ያበረታታንን የክልሉን መንግስት ከልብ በሕዝባችን ስም አመሰግናለሁ" የይርጋጨፌ ቡና ስፖርት ክለብ በሴቶች እግር ኳስ በ2017 ዓ.ም ባደረገው እንቅስቃሴ ከ...
12/05/2026

" ለመጣው ውጤት እውቅና በመስጠት ያበረታታንን የክልሉን መንግስት ከልብ በሕዝባችን ስም አመሰግናለሁ"

የይርጋጨፌ ቡና ስፖርት ክለብ በሴቶች እግር ኳስ በ2017 ዓ.ም ባደረገው እንቅስቃሴ ከከፍተኛ ሊግ ወደ ፕሪሚየር ሊግ በማደጉ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በዛሬው ቀን ለክለቡ አንድ የማመላለሻ አውቶብስና ለማበረታቻ የሚሆን 1 ሚሊዮን ብር ተበርክቶልናል።

ለዚህ ስኬት ያበቃንን ፈጣሪ እያመሰገኩ በታላቅ ተጋድሎ ውጤቱን በማስመዝገብ ዞናችንንና ክልላችንን ከፍ ያደረጉ ተጫዋቾች ፣ ኮቺንግ ስታፍ እንዲሁም ለክለቡ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ አስፈላጊውን የተወጡ የዞን መንግስትና የክለቡ ቦርድ አካላት ምስጋና ይገባቸዋል ።

በመጨረሻም ለመጣው ውጤት እውቅና በመስጠት ያበረታታንን የክልሉን መንግስት ከልብ በሕዝባችን ስም አመሰግናለሁ።

የጌዴኦ ዞን ም/አስተዳደር እና የክለቡ ቦርድ ሰብሳቢ
አቶ ተገኝ ታደሴ

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) የክልሉ መንግስት ለይርጋጨፌ ቡና ሴቶች እግር ኳስ ክለብ ላበረከቱት የአውቶቢስና የገንዘብ ሽልማት ምስጋናቸውን አቀረቡ ‎‎ዲላ ፦ግንቦት 4/2...
12/05/2026

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) የክልሉ መንግስት ለይርጋጨፌ ቡና ሴቶች እግር ኳስ ክለብ ላበረከቱት የአውቶቢስና የገንዘብ ሽልማት ምስጋናቸውን አቀረቡ

‎ዲላ ፦ግንቦት 4/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን )

‎የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ለይርጋጨፌ ቡና ሴቶች እግር ኳስ ክለብ ላበረከቱት የአውቶቢስና የገንዘብ ሽልማት ለክልሉ መንግስት ምስጋናቸውን አቅርቧል ።

‎የደቡብ ኢትዮጽያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በዛሬዉ እለት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስፖርት ምክር ቤት ወደ ፕሪሚየር ሊግ ላደጉ ክለቦች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት መርሃ ግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ አካሂዶ ለይርጋጨፌ ቡና ሴቶች እግር ኳስ ክለብ ድጋፉን አበርክቷል ።

‎በእዚህም መሠረት ወደ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ በማደግ በዘንድሮው አመት ተሳትፎ እያደረገ የሚገኘው የይርጋጨፌ ቡና ሴቶች እግር ኳስ ክለብ አንድ አውቶቢስ እና የአንድ ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል ።

‎ለይርጋጨፌ ቡና ሴቶች እግር ኳስ ክለብ ለተበረከተለት የማበረታቻ ሽልማት በዞኑ ስም ምስጋናቸውን ያቀረቡት
‎የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ቡድኑ የተለያዩ ፈተናዎችን በትጋትና በጽናት በመሻገር ለውጤት በመብቃቱ ለተበረከተለት ድጋፍ ምስጋናቸውን ለክልሉ መንግስት አቅርበዋል ።

የክልሉ መንግስት ለይርጋጨፌ ቡና ሴቶች ቡድን የማመላለሻ አውቶቢስ እና የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓልበሴቶች ክለብ ውድድር እምብዛም ትኩረት ባልተሰጠበት የይርጋጨፌ ቡና ሴቶችን ቡድን  ...
12/05/2026

የክልሉ መንግስት ለይርጋጨፌ ቡና ሴቶች ቡድን የማመላለሻ አውቶቢስ እና የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል

በሴቶች ክለብ ውድድር እምብዛም ትኩረት ባልተሰጠበት የይርጋጨፌ ቡና ሴቶችን ቡድን በፅናት ፈተናዎችን በመቋቋም ወደ ፕሪሜርሊጉ በመቀላቀል ላበረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።

እግር ኳስ ሀይል የሚሰበስብ፣ ግዚያዊ እና ወቅታዊ ፈተናዎችን የሚያሻግር ዘርፍ ስለሆኑ በክልሉ ያሉ ክለቦች በመደጋገፍ ፣ ወድማማችንትን በማጠናከር በጋራ ተጋግዘው በፕሪሊሜር ሊጉ ጠንካራ ክለብ በመሆን ለስኬት ሊበቁ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ቀጣይ ተኪ ወጣቶችን በማፍራት ዙሪያ በቅርበት ከአመራሩ ጋር በመስራት እና ጠንክሮ በመስራት በፕሪሜርሊጉ መቆየት ብቻ ሳይሆን የዋንጫ ባለቤት ስኬታማ እንዲሆን መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

ክለቦች በኢኮኖሚ ጠንካራ ካልሆኑ ሊወዳደሩ አይችሉም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ጠንካራ የደጋፊዎች ማህበር በመመስረት የክለቡን የኢኮኖሚ አቅም ማጠናከር ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተናግረዋል።

የክልሉ መንግስት የማመላለሻ አውቶቢስ እና የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው በቀጣይ አስፈላጊው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል

ለጋሞ ጨንቻ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን እና ለፕሪሜር ሊግ ተሳታፊዎቹ ለይርጋጨፌ ቡና የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የዕውቅናና የሽልማት ስነስርዓት በመካሄድ ላይ ይገኛል ግንቦት 04/2018 ዓ.ም...
12/05/2026

ለጋሞ ጨንቻ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን እና ለፕሪሜር ሊግ ተሳታፊዎቹ ለይርጋጨፌ ቡና የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የዕውቅናና የሽልማት ስነስርዓት በመካሄድ ላይ ይገኛል

ግንቦት 04/2018 ዓ.ም

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ለጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ እና ለፕሪሜር ሊግ ተሳታፊዎቹ ለይርጋጨፌ ቡና የሴቶች እግር ኳስ ክለብ የዕውቅና እና የማበረተቻ የሽልማት ስነስርዓት በወላይታ ሶዶ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የዋንጫ ተፋላሚ በመሆን ፕሪሜሪ ሊጉን መቀላቀሉን ላረጋገጠው ለጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ቡድን እና በሴቶች ፕሪሜር ሊግ የክልላችን ብቸኛ ተሳታፊ ለሆነው ለይርጋጨፌ ቡና የሴቶች ቡድን በክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ ዕውቅናና ሽልማት የሚበረከት ይሆናል።

የክልሉ መንግስት ክልሉ በርካታ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ካለው እምቅ አቅም አንጻር እንዲሁም ስፖርት የህዝቦች ትስስርን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና ለጤናማ ህብረተሰብ ግንባታ ካለው ከፍተኛ ፋይዳ አኳያ ለዘርፉ ዕድገት አበክሮ በመስራት ላይ ይገኛል።

በዚህ ረገድ ክልሉን በመወከል በሀገር አቀፍ ውድድሮች የሚሳተፉ ክለቦች መበራከት በክልሉ የስፖርቱን ዘርፍ በማነቃቃት ለዘርፉ ዕድገት የሚደረገውን ጥረት ከማገዝ ባለፈ ብቃት ያላቸው ስፖርተኞችን ለማፍራት ለሚደረገው ጥረት ውጤታማነት ፋይዳው የጎላ ነው።

ለዚህም የክልሉ መንግስት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ለሚሳታፉ ክለቦች ዕውቅናና ማበረታቻ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፥ በዛሬው ዕለትም ለሁለቱ እግር ኳስ ክለቦች ዕውቅናና ማበረታቻ የሚሰጥ ይሆናል።

ጋሞ ጨንቻ በቀጣይ የ2019 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ከወላይታ ዲቻ እና አርባምንጭ ከነማ እግር ኳስ ክለቦች በተጨማሪ ከደቡብ ኢትዮጲያ ክልል በውድድሩ የሚሳተፍ ሦሥተኛው ክለብ ይሆናል።

የይርጋጨፌ ቡና የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በተመሳሳይ የክልላችን ብቸኛው ተወካይ በመሆን ለዋንጫው የሚፎካከር ከመሆኑም በላይ ለሴቶች የስፖርት ተሳትፎ ዕድገት ከፍተኛ ተነሳሽነት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።

የይርጋጨፌ ቡና እና ሲዳማ ቡና ተጠባቂ ጨዋታ ግብ ሳይቆጠርበት ተጠናቋልግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ምይርጋጨፌ ቡና እና ሲዳማ ቡና በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ያደረጉት የ26ኛ ሳምንት የኢት...
10/05/2026

የይርጋጨፌ ቡና እና ሲዳማ ቡና ተጠባቂ ጨዋታ ግብ ሳይቆጠርበት ተጠናቋል

ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም

ይርጋጨፌ ቡና እና ሲዳማ ቡና በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ያደረጉት የ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ግብ ሳይቆጠርበት ተጠናቋል።

ይርጋጨፌ ቡና አንድ ነጥብ ማግኘቱን ተከትሎ ከወራጅ ቀጠና በሰፊ ነጥብ ልዩነት ርቆ ይገኛል::

በጨዋታው ሰላማዊት ብርሃኑ ኮከብ ተጫዋች በመሆን ተመርጣለች::

ቡናዎቹ የውድድር አመቱ የመጨረሻ ጨዋታ ከሸገር ከተማ ጋር የምያደርጉ ይሆናል::

  በማለት  የጌዴኦ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ያሬድ በ2 ሺህ ብር ቻሌንጁን ተቀላቅሏለች::እናመሰግናለን🙏🙏🙏
09/05/2026

በማለት የጌዴኦ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ያሬድ በ2 ሺህ ብር ቻሌንጁን ተቀላቅሏለች::

እናመሰግናለን🙏🙏🙏

30/04/2026

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 23ኛ ሳምንት የሦስተኛ ቀን 7:00 ጨዋታ

ኢትዮ ኤሌክትሪክ 2-1 ይርጋጨፌ ቡና

ይርጋጨፌ ቡናን ወደ 2019 የኢትጵያ ከፍተኛ ሊግ ማሳደግ የቻለው አሰልጣኝ ኢዮብ ዋቤሚያዝያ 20/2018 ዓ.ምየነበረው ጉዞ በጣም ረጂም ጉዞ ነው ብዙም በማይመቹ ሜዳዎች ነው ሁለቱንም ዙር ...
28/04/2026

ይርጋጨፌ ቡናን ወደ 2019 የኢትጵያ ከፍተኛ ሊግ ማሳደግ የቻለው አሰልጣኝ ኢዮብ ዋቤ

ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም

የነበረው ጉዞ በጣም ረጂም ጉዞ ነው ብዙም በማይመቹ ሜዳዎች ነው ሁለቱንም ዙር ጨዋታዎችን ያደረግነው በበርካታ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፈን የምንፈልገውን ውጤት አስመዝግበናል ሲል ተናግሯል።

ይርጋጨፌ ቡና ከዝህ በፊት ብዙ ታላላቅ ተጨዋቾችን ያፈራ ቡድን ነው ዞኑ ወደ ከፍተኛ ሊግ እንድናግድግ የተሻለ ሥራዎችን ሰርቷል ለዛም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ወደ ከፍተኛ ሊግ ያደግነው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ተጫውተን ነው እጅግ ከባድ ነበር ጨዋታው ግን በፈጣሪ እርዳታ ወደ ከፍተኛ ሊግ አድገናል ለዝህም ከጎኔ ለነበሩ የአሰልጣኝ ቡድን አባላት ፣ ለዞኑ አመራሮች እና ለክለቡ ተጨዋቾችን ለማመስገን እፈልጋለው ሲል ገልጿል።

ዋና አሰልጣኝ ኢዮብ ዋቤ በሚቀጥለው ዓመት ክለቡን ወደ 2020 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ለማሳደግ የተሻለ ቡድን ይዘን እንቀርባለን የአከባቢው ባለሀብት እንድሁም አመራሮች ለዝህ ከወድሁ ሥራ እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

አሰጋኸኝ ጉዬ የይርጋጨፌ ቡና እግር ኳስ ክለብ ሥራ አስኪያጂ እንደገለፁት በመጀመሪያ ዝግጅታቸውን አርፍደው እንደጀመሩና የዋና አሰልጣኝ ቅጥር ተጨዋቾችም በአጭር ጊዜ መሰባሰባቸው ገልፀው ከሁለት ዓመት በፊት ክለቡ ከከፍተኛ ሊግ ይርጋጨፌ ቡና ሲወርድ ከፍተኛ የበጀት እጥረት ዋነኛው የክለቡ ውድቅ ምልክት እንደነበረ ገልፀው አሁን ግን ክለቡ ከቦርድ ጀምሮ እንደ አዲስ በመዋቀሩ የተሻለ ውጤት መቷል ሲል ገልጾ በሚቀጥለው ዓመቱ ክለቡ ወደ ፕሪምየር ሊግ እንዲያድግ ከወድሁ ዞኑም የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግሯል።

  ማለት  የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዘርሁን ማሞ በ5 ሺህ ብር ቻሌንጁን ተቀላቅሏል::እናመሰግናለን🙏🙏🙏
27/04/2026

ማለት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዘርሁን ማሞ በ5 ሺህ ብር ቻሌንጁን ተቀላቅሏል::

እናመሰግናለን🙏🙏🙏

Address

ስታዲየም ሰፈር
Dilla

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ይርጋጨፌ ቡና ስፖርት ክለብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share