ሀገሬ

ሀገሬ የአንዱ ነገር መጨረሻ የሌላው ነገር መጀመሪያ ነው ።

 🕊የትግራይ ክልል አመራሮችና ፓለቲከኞች አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት የተጀመረውን ሰላም እንዲያፀኑና ከዳር እንዲያደርሱ ተማፅኖ ቀረበ።ተማፅኖ ያቀረቡት ከ12 ክልሎችና የከተማ አስተዳደ...
28/07/2025

🕊

የትግራይ ክልል አመራሮችና ፓለቲከኞች አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት የተጀመረውን ሰላም እንዲያፀኑና ከዳር እንዲያደርሱ ተማፅኖ ቀረበ።

ተማፅኖ ያቀረቡት ከ12 ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ናቸው።

ቁጥራቸው 50 የሆኑት መላ የኢትዮጵያ ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የወከሉ የሰላም ልኡካን ዛሬ ሀምሌ 21/2017 ዓ.ም ጠዋት መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ሰዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከአውሮፕላን ማረፍያ ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ቦታ ያቀኑት የሰላም ልኡካኑ ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደና እና ካቢኔያቸው በተገኙበት በየእምነታቸው ፀሎት አድርሰዋል።

የክልሉ አመራሮችና ፓለቲከኞችም ለተሻለ ሰላምና አገራዊ መረጋጋት አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት ተጨማሪ ግጭት እንዲያስቀሩ አባታዊና ሃይማኖታዊ ምክርና ተማፅኖ ቀርበውላቸዋል።

የሰላም ልኡካኑ ከጦርነቱ በፊት ወደ ትግራይ ተመላልሰው ያደረጉት ጥረት ግጭቱ ማስቀረት ባለመቻሉ በቁጭት አስታውሰው ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ ለሦሥተኛ ጊዜ መምጣታቸውና የሰላም ጥረታቸው ሳይታክቱ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

" የጀመረው ሰላም እንዲፀና ፤ ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከመስራትና ከመጣር የበለጠ ሃይማኖታዊና አባታዊ ተልእኮ የለንም ለዚህም የሚከፈለውን ሁሉም ዓይነት መስዋእትነት እንከፍላለን " ብለዋል።

የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና ካቢኔያቸው ፣ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት፣ የተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ስቪክ ማህበራት እንደሚወያዩ ከወጣው መርሀ ግብር ሐመረዳት ተችሏል።

የሀገሬ ልጅ
06/05/2025

የሀገሬ ልጅ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ምን ተስማሙ ?በቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ስምምነት ላይ...
13/12/2024

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ምን ተስማሙ ?

በቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ስምምነቱ " የአንካራ ስምምነት " ተብሏል።

ይህ ተከትሎ በወጣው የስምምነት ሰነድ የተስማሙባቸው ጉዳዮች በዝርዝር ተቀምጠዋል።

ምንድናቸው ?

➡️ የሶማሊያ እና የኢትዮጵያ መሪዎች አንዳቸው ለሌላኛቸውን ሉዓላዊነት ፣ አንድነት ፣ነፃነት እና የግዛት አንድነት ለማክበር ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።

➡️ በወዳጅነት እና በመከባበር መንፈስ ልዩነቶችን እና አከራካሪ ጉዳዮችን በመተው ፤ በመተጋገዝ ለጋራ ብልጽግና ለመስራት ተስማምተዋል።

➡️ ሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለከፈሉት መስዋዕትነት እውቅና ሰጥታለች።

➡️ ኢትዮጵያ የሶማሊያን የግዛት አንድነት ባከበረ ሁኔታ የባህር በር ተጠቃሚ መሆኗ / ወደ ባህር እና ' ከ ' ባህር / ሊያስገኝ የሚችለው ልዩ ልዩ ጥቅም ላይ ተማምነውበታል።

➡️ ሁለቱንም ተጠቃሚ ባደረገ ሁኔታ የንግድ ውል ይታሰራል።

➡️ ኢትዮጵያ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና እና ቀጣይነት ያለው / ዘላቂ የባህር በር መዳረሻ / አክሰስ እንዲኖራት ስምምነት ላይ ተደርሷል ፤ ይህም በሉዓላዊ የሶማሊያ መንግሥት ስልጣን ስር የሚተገበር ነው።

ለዚህም የሚሆን ፦
- የኮንትራንት
- የሊዝ ውልን ጨምሮ ሌሎች ሞዳሊቲዎች ላይ በቀጣይ በቅርበት አብሮ ለመስራትና ለማጠናቀቅ ተስማምተዋል።

ለነዚህ ዓላማዎች መሳካት በጥሩ እምነት ከየካቲት 2025 መጨረሻ በፊት የቴክኒካል ድርድር ለመጀመር ወስነዋል። ይህም በቱርክ አመቻችነት የሚሳለጥ ሲሆን በ4 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ስምምነት ይፈረማል።

ለዚህም ቁርጠኝነትና ለቃል ኪዳኑ ተግባራዊ መደረግ የቱርክን እገዛ በደስታ ተቀብለዋል።

➡️ በአተገባበር ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት እና በሰላማዊ መንገድ ' እንደአስፈላጊነቱ ' በቱርክ ድጋፍ ለመፍታት ቃል ገብተዋል።

 " አልፀፀትም " / " HIN GAABBU "በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የገዘፈ ስም ካላቸው ፖለቲከኞች አንዱ የሆኑት የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ መፅሀፍ ይዘው እየመጡ እንደሆ...
13/12/2024



" አልፀፀትም " / " HIN GAABBU "

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የገዘፈ ስም ካላቸው ፖለቲከኞች አንዱ የሆኑት የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ መፅሀፍ ይዘው እየመጡ እንደሆነ ገለጹ።

የኢህአዴግን ስርዓት በሰላማዊ መንገድ በመታገል ስርዓቱ ሳይወድ በግዱ እንዲቀየር በማድረጉ ረገድ ግንባር ቀደሙን ድርሻ እንደሚይዙ የሚነገርላቸው አቶ ጃዋር መሀመድ ከዚህ ቀደም ሰፋ ያለ መፅሀፍ እየጻፉ እንደነበር መግለፃቸው ይታወሳል።

በመጨረሻም መፅሀፋቸው መጠናቀቁን እና ለአንባቢያ ሊደርስ መሆኑን አሳውቀዋል።

በቀጣይ ሳምንት ኬንያ፣ ናይሮቢ ውስጥ በሚዘጋጅ ዝግጅት መፅሀፉ ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።

" አልፀፀትም " / " HIN GAABBU " በሚል ርዕስ የተዘጋጀው መፅሀፋቸው በርካታ እና ከዚህ ቀደም ይፋ ያላደረጓቸው ጉዳዮች የተዳሰሰበት እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረዳት ችሏል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ፦
° በኢትዮጵያ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል የገዘፈ ስም ያላቸው ፤
° አሜሪካ ሆነው የኢህአዴግን ስርዓት በሰላማዊ ትግል በመጣሉ በኩል ቁልፍ ሚና የነበራቸው ፤
° ' ለውጥ መጣ ' ተብሎ ወደ ሀገር ከገቡ በኃላ የሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ ከቀብር ጋር በተያያዘ በተፈጠረው ሁኔታ ታስረው ለበርካታ ወራት በእስር ቆየተው መፈታታቸው ይታወሳል።

ፖለቲከኛው ከእስር ቤት ቆይታ በኃላ ቀድሞ የሚታወቁባቸውን ኃይለኛ ንግግሮችን እና ፅሁፎችን በመተው ዝምታን መርጠው ብዙ ጊዜያቸውን በመፅሀፍ ዝግጅት ላይ እንዲሁም በሀገሪቱ ያሉ ግጭቶች እንዲቆሙ የድርሻቸውን የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸው ይነገራል።

ከእስር በኃላ ኢትዮጵያ እንዲሁም ኬንያ ናይሮቢ እየተመላለሱ የሚኖሩ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜያቸውን ግን ናይሮቢ ናቸው።

በኬንያ ፣ ናይሮቢ ገቢ የሚያገኙባቸውን ስራዎች ከመስራት ባለፈ እንደ ኢትዮጵያ ብዙ ሰዎች ሊያገኟቸው / ሊጠይቋቸው ስለማይመጡ በጥሞና ለማሰብ፣ ለማንበብ እና መፅሀፋቸውን ለማዘጋጀት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ለመረዳት ተችሏል።

" አልፀፀትም / HIN GAABBU " የተሰኘው መፅሀፋቸው ቀጣይ ሳምንት ሀሙስ ናይሮቢ ውስጥ ላውንች ይደረጋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በአለባበስ ምክንያት የታገዱ ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጠይቋል።በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍ...
30/10/2024

በአዲስ አበባ ከተማ በአለባበስ ምክንያት የታገዱ ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጠይቋል።

በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በሚገኙ አራት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሙስሊም ተማሪዎች “በኒቃባቸው ምክንያት” ከትምህርት ገበታ መታገዳቸው በሚዲያዎች ሲሰራጭ ቆይቷል።

ይህን ተከትሎ ምክር ቤቱ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ትናንት በጻፈው ደብዳቤ፤ ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ በአዲስ አበባ በሚገኙ እንዳንድ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ በአለባበሳቸው ምክንያት “ጫናና እንግልት” እየደረሰ ነው ብሏል::

በአዲሱ ስርአተ ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ መማርን የሚመለከተው አንቀጽ ተቃውሞ ገጠመው በዛሬው ዕለት የተካሄደው የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር-ቤት ጉባኤ የተለያዩ አዳዲስ ረቂቅ አዋጆችን ለዝር...
29/10/2024

በአዲሱ ስርአተ ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ መማርን የሚመለከተው አንቀጽ ተቃውሞ ገጠመው

በዛሬው ዕለት የተካሄደው የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር-ቤት ጉባኤ የተለያዩ አዳዲስ ረቂቅ አዋጆችን ለዝርዝር ዕያታ ወደ ቋሚ ኮሚቴዎች ልኳል።

ከቀረቡለት አዋጆች መካከል የትምህርት ስርአቱን የሚመለከተው ረቂቅ አዋጅ አንዱ ነው። በዚህ አዋጅ የአፍ መፍቻ ቋንቋን የተመለከተው ረቂቅ አዋጅ ይገኝበታል።

የአፍ መፍቻ ቋንቋን በትምህርት ስርአቱ ውስጥ መገልገል ስለሚቻልበት ሁኔታ የሚያብራራው የረቂቅ አዋጁ፤ ከዚህ በፊትም ጥያቄ፣ አስተያየት እና ተቃውሞ ሲያስተናግድ እንደቆየ ይታወሳል፡፡

የመንግስት ተጠሪ ሚንስትር ተስፋዬ በልጅጌ በንባብ ያቀረቡት አዲሱ የትምህርት ስርዓት ረቂቅ አዋጅ በርከት ያሉ ሃሰቦች እና አስተያየቶች ተሰንዝሮበታል።

በተለይም በትምህርት ስርዓቱ የሀገር ውስጥ ቋንቋ ረገድ ረቂቅ አዋጁ የሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ በትኩረት እንዲመለከተው የምክር ቤት አባላቱ አሳስበዋል።

ምክር ቤቱ የምክር ቤት አባላቱ ያነሷቸውን ጥያቄዎች አዳምጦ የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን በአንድ ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ በማጽደቅ ለዝርዝር ዕይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል፡፡(አሐዱ)

" ሲሾሙ ' ወጣት ፣ በትምህርት ዝግጅታቸው ጥሩ '  ተብሎ ይሾማል ሲወርዱ ግን በምን ፐርፎርም እንዳደረጉና እንዳላደረጉ አይነገረንም " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባ...
29/10/2024

" ሲሾሙ ' ወጣት ፣ በትምህርት ዝግጅታቸው ጥሩ ' ተብሎ ይሾማል ሲወርዱ ግን በምን ፐርፎርም እንዳደረጉና እንዳላደረጉ አይነገረንም " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባሉ እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተመራጩ ደሳለም ጫኔ (ዶ/ር) ከሚሰጡ ሹመቶች ጋር በተያያዘ ያላቸውን ጥያቄ በምክር ቤት አንስተዋል።

ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ፥ " የሚነሱ ሚኒስትሮች ከሾናቸው በኃላ ምን አጉለው እንደተነሱ ፤ ምን ድክመት እንዳሳዩ ፤ ወይ ምን የስነምግባር ጥሰት እንዳሳዩ አይቀርብም ፤ በተጨማሪም እነሱን የሚታኳቸው ሚኒስትሮች ከነሱ በምን እንደሚሻሉ አይነገረም " ብለዋል።

" እርግጥ ሲሾሙ ' ወጣት ፣ በትምህርት ዝግጅታቸው ጥሩ ' ምናም ተብሎ ይሾማል ሲወርዱ ግን በምን ፐርፎርም እንዳደረጉ በምን ፐርፎርም እንዳላደረጉ አነገረንም። " ሲሉ ገልጸዋል።

ይህ ከግልጽነት እና ከተጠያቂነት መርህ አንጻር ጥያቄ እየሚያስነሳ እንደሆነ አስገንዝበዋል።

ሚኒስትሮች ከቦታቸው ሲወርዱ ለምን በምን ምክንያት እንደወረዱ ፤ በምትካቸው የሚመጡትም ከነሱ በምን እንደሚሻሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ፤ ምክር ቤቱም ማወቅ የለበትም ? ሲሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ጠይቀዋል።

2016 ን በአንድ ቃል ግለፁት ብትባሉ ምን ትሉታላቹ 🙂  እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
10/09/2024

2016 ን በአንድ ቃል ግለፁት ብትባሉ ምን ትሉታላቹ 🙂 እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።

 አትሌቲክሳችን ስር ነቀል ለውጥ ያስፈልገዋል። ይህ መሆን ያለበት ደግሞ በትክክለኛ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ነው።የኦሎምፒክ ውጤቱ አንገት የሚያስደፋ ነው። በጭቅጭቅ፣ በንትርክ፣ በየሚዲያ ላ...
13/08/2024



አትሌቲክሳችን ስር ነቀል ለውጥ ያስፈልገዋል። ይህ መሆን ያለበት ደግሞ በትክክለኛ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ነው።

የኦሎምፒክ ውጤቱ አንገት የሚያስደፋ ነው።

በጭቅጭቅ፣ በንትርክ፣ በየሚዲያ ላይ በሚደረግ ምልልስ የተጀመረው የፓሪስ ውድድር ኢትዮጵያን የማይመጥን እጅግ ዝቅ ያለ ውጤት ተመዝግቦበት አልቋል።

ጥፋት ከደረሰ እና ውጤት ከጠፋ በኃላ የሚቀርብ ይቅርታ ተቀባይነት የለውም።

የሚያስፈልገው ሁሉም የአትሌቲክሱ ቤተሰብ ቁጭ ብሎ በእርጋታ መክሮ ፤ ስር ነቀል ለውጥ ማምጣት ብቻ ነው።

ሁሉም ዜጋ በየፊናው የተሰማውን ብስጭት፣ ንዴት እየገለጸ ነው። ይህ የሚጠበቅ ነው። ምክንያት ? ሀገሩ ነው፣ ክብሩ ነው። የሚጠብቀውን ሳያገኝ ሲቀር ህዝቡ ያዝናል ፣ይበሳጫል።

እውነትም " ለሀገራችን ክብርና ፍቅር አለን " የሚሉ የአትሌቲክሱ አካላት በእርጋታ ፣ በንግግር ችግሮች እንዲፈቱ ያድርጉ።

ይህም በመሪዎች እና አመራሮች ደረጃ " ለጠፋው ውጤት ፣ ዝቅ ላለው የህዝባችን ክብር ኃላፊነት እንወስዳለን ፤ ይህ የመጣው ስላልሰራን ነው " ብሎ ቦታ መልቀቅን ፤ ለሌላው እድል መስጠትን ያካትታል።

በአትሌቶች ዘንድም የውጤታችን መጥፋት እንዴት እንደተከሰተ ፤ ምናልባት የተሻሉ አትሌቶችም ካሉ ለነሱ ቦታ እያስረከቡ መሄድም እንዲቻል በጥልቀት መገምገም ይገባል።

በአትሌቶች እና አሰልጣኞች መካከልም ተግባብቶ እንደ አንድ ሀገር ዜጋ በቡድን አለመስራት ችግርም ካለ መፈተሽ አለበት።

ከምንም በላይ ግን ዘርፉን የሚመሩትን አካላት እና እዛ አካባቢ ያሉትን በሙሉ በጥልቀት መገምገም ይገባል።

በአጠቃላይ ስር ነቀል ለውጥ መምጣት አለበት።

ህዝቡ የሚፈልገው ክብሩ እንዲመለስለት ብቻ ነው ፤ ሙያውን የሚያውቅ በቦታው ተገኝቶ ለውጥ አምጥቶ በሀገሩ ውጤት ተደስቶ ማየት ነው።

የሚዲያ ምልልስ ፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ በዚህ መሃል ደግሞ የሚፈጠር የውጤት ውድቀት ህዝብን ፍጹም አይመጥንም።

ጉዳዩ ሙያዊነውና ለባለሙያዎቹ እንተወው ፤ እውነት ግን " የሀገራችን ክብር ይመለከተናል " የሚሉ የሀገር ጉዳይ ብቻ አላማቸው ከሆነ ሌላ ፍላጎት ከሌላቸው ጭቅጭቅ እና ንትርክ ትተው ቁጭ ብለው መነጋገር አለባቸው። ኃላፊነት መውሰድም አለባቸው።

በአሁኑ ውጤት ያልተበሳጨ፣ ያላዘነ ፣ አንጀቱ ያላረረ ዜጋ የለም በዚህም ደግሞ በስሜታዊነት አስተያየቱን እየሰጠ ነው። ለውጥ እንዲመጣ ወደ ክብራችን እንድንመለስ ጥያቄ እያቀረበ ነው።

ነገር ግን አንዳንድ አስተያየቶችም ጥንቃቄ ይፈልጋሉ የአትሌቶችን ስነልቦና እንዳይጎዳ።

ባለፈው የአትሌቲክስ ሻምፒዮና " ያለእናተ ሰው የለም ፤ ጀግኖች " እያልን ያወደስናቸውን ልጆች ዛሬ ውጤት በመጥፋቱ በብስጭት እና ሀዘን ስሜት ያልተገባ ቃል እንዳንናገር መጠንቀቅ ይገባል።

ዳግም ህዝቡ በሚኮራበት #አትሌቲክስ እንዳያዝን እና እንዳይበሳጭ ተነጋግሮ ስር ነቀል ለውጥ መምጣት አለበት።

ህዝቡ በአትሌቲክሱ ዘርፍ ክብሩ እንዲመለስለት ይፈልጋል፤ አራት ነጥብ !

ስር ነቀል ለውጥ ለኢትዮጵያ 🇪🇹 አትሌቲክስ !

25/07/2024

#ጎፋ
ልብ ሰባሪ💔🖤 #ሼር በማድረግ እንተባበር
በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ቀበሌ በጎርፍ አደጋ ለተፈናቀሉና ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች የድጋፍ ማሰባሰቢያ በዞኑ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት ይፋ የተደረገው መሆኑን እንገልጻለን።

በዞኑ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት ማቋቋሚያ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000511561276 ይሄ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።
#ጎፋ

ደግሞ ሌላ ትኩሳት 😪የመሬት መሰንጠቅ ና የመሬት ናዳ በቤንች ሸኮ ዞን 😪⏩ 28 ቤቶች የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ደርሶባቸዋል !⏩ 208 ሰዎች ከቤታቸው ተፈናቅለዋል !በደቡብ ምዕራብ ኢት...
25/07/2024

ደግሞ ሌላ ትኩሳት 😪

የመሬት መሰንጠቅ ና የመሬት ናዳ በቤንች ሸኮ ዞን 😪

⏩ 28 ቤቶች የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ደርሶባቸዋል !
⏩ 208 ሰዎች ከቤታቸው ተፈናቅለዋል !

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ ና መሰንጠቅ 208 ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል።

ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በከፍተኛ አደጋ ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውም ተገልጿል።

የክረምቱ የዝናብ መጠን መጨመር ጋር ተያይዞ በሰሜን ቤንች ወረዳ ቃሻ ፣ ሙያ ኬላና ዋላ ቀበሌዎች ከፍተኛ የሆነ የመሬት መሰንጠቅና ናዳ ተከስቷል !

ትላንት ማምሻውንና ዛሬን ጨምሮ በ3 ቀበሌዎች ሰሞኑን በተከታታይ በጣለው ዝናብ 28 የመኖሪያ ቤቶች የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ደርሶባቸዋል። እንዲሁም በቀበሌዎቹ የበቆሎ ፣ እንሰት ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ማሳዎች በናዳው ወድመዋል።

እስካሁን 208 ለአደጋ ተጋላጭ ሰዎችን ከስፍራው በማውጣት በቀሌዎች ግቢ ፣ በቤተክርስቲያንና ወደ ዘመዶቻቸው የማዘዋወር ስራ ተሰርቷል

የዝናብ መጠኑ የሚቀጥል ከሆኑ በወረዳው ተጨማሪ 4 ቀበሌዎች በከፍተኛ አደጋ ውስጥ ናቸው 😪

ዋላ ቀበሌ አካባቢ ከዋቻ ማጂ - ማጂ በሚወስደው የአስፓልት መንገድ ላይ የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ ተከስቷል የሚመለከታቸው አካላት በፍጥነት የጥገና ስራ ካልሰሩ የትራንስፖርት አገልግሎቱ ሊቋረጥ ይችላል !

እንደ ዞን ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በቅጽበታዊ ጎርፍ መጥለቅለቅ ፣ የመሬት መሰንጠቅና የናዳ ችግር ውስጥ ናቸው

በተለይ ሚዛን አማን ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የቅድመ ማስጠንቀቂያ ስራ ሊሰራ ይገባል ።

እስካሁን በሰውና በእንሳት ላይ የደረሰ አደጋ የለም ! በሰሜን ቤንች ወረዳ ተጋላጭ በሆኑ 7 ቀበሌዎች ህጻናት ወደ ማሳ እንዳይሄዱ ማድረግ ፣ አርሶ አደሩም እንስሳትን ወደ ግጦሽ ይዞ እንዳይሄድ የቅስቀሳና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተሰራ መሆኑን የቤንች ሸኮ ኮሙኒኬሽን ዘግበዋል ።

Address

Dessie

Telephone

+251925213962

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሀገሬ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሀገሬ:

Share