South wollo sports

South wollo sports south wollo zone sports

25/03/2026
የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በየደቡብ ወሎ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ የአካል ድጋፍ አከናወነ።🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹📍 ደሴ | መጋቢት 9/20...
18/03/2026

የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በየደቡብ ወሎ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ የአካል ድጋፍ አከናወነ።
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

📍 ደሴ | መጋቢት 9/2018 ዓ.ም

#የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በደቡብ ወሎ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ በአካል በመገኘት የአካል ድጋፍ አድርጓል።
በድጋፉ ወቅት ቢሮው በ2018 ዓ.ም የበጀት አመት እስከዚህ ወር ድረስ የተከናወኑ ስራዎችን በመረጃ መሰረት በመገምገም ከፍተኛ አፈጻጸም ያሳዩ ተግባራትን አድናቆት አቀርቧል።

በተጨማሪም ያልተጠናቀቁ ስራዎች በቀጣይ ወቅት ትኩረት እንዲሰጣቸው አቅጣጫ ተሰጥቶ፣ እንዲፈጸሙ አስፈላጊ የቴክኒክና የአመራር ድጋፍ ተደርጓል።
በስራ ሂደት ውስጥ የተገኙ ችግሮች በኃላፊዎች ቀርበው በተደረገ ምክክር ውይይት ላይ ተመልከተው፣ ተገቢ መፍትሄዎችና አቅጣጫዎች ተጠቁመዋል።
ቢሮው ይህ ድጋፍ ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን በማስገንዘብ፣ የመምሪያውን የስራ አፈጻጸም ለማሻሻል አስፈላጊ ሚና እንዳለው ገልጿል።

📣 “ወቅቱን የጠበቀ ድጋፍ ለላቀ አፈጻጸም!”

ⓒ ደቡብ ወሎን ይጎብኙ!
የደቡብ ወሎ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ

07/03/2026
23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች በደቡብ ወሎ አጠቃላይ አሸናፊነት ተጠናቀቀየካቲት 26/2018 ዓ.ም.ደሴበደሴ ከተማ ሲካሄድ በነበረው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር በዛሬው እ...
05/03/2026

23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች በደቡብ ወሎ አጠቃላይ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የካቲት 26/2018 ዓ.ም.
ደሴ
በደሴ ከተማ ሲካሄድ በነበረው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር በዛሬው እለት ፍጻሜውን አግኝቷል
በውድድሩም በርካታ ስፖርተኞችን ይዞ የተሳተፈው ደቡብ ወሎ በአጠቃላይ አሽናፊ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ የ7 ዋንጫ ባለቤትም ሆኗል።
👉 በገና ውድድር 1ኛ የወርቅና ዋንጫ ተሸላሚ
👉 በቀስት ስፖርት በወንዶች የወርቅና ዋንጫ ተሸላሚ
👉 በቀስት ስፖርት በሴቶች የወርቅና ዋንጫ ተሸላሚ
👉 በሻህ ስፖርት በወንዶች የወርቅና ዋንጫ ተሸላሚ
👉 በቀስት ድብልቅ የወርቅና ዋንጫ ተሸላሚ
👉 በቡብ ወንዶች የወርቅና ዋንጫ ተሸላሚ
👉 በአጠቃለይ የዋንጫ ተሸላሚ
👉 በትግል በሁለቱም ጾታ 2ኛ ደረጃ
👉 በገበጣ ወንድ የብር ሜዳልያ
👉 በቡብ ሴት የነሀስ ሜዳልያ
👉 በሻህ ሴት የብር ሜዳልያ
በማግኘት ዞናችን በስኬት አጠናቋል።
በውድድሩ ደሴ ከተማ አስተዳደር 2ኛ ደረጃ ሲሆን ሰሜን ሸዋ ዞን 3ኛ በመሆን ተጠናቋል።
በውድድሩ የመጣው ውጤት በጣም እንዳስደሰታትና በቀጣይ በርካታ ስራዎችን ለመስራት አቅም እንደሚሆን የገለጹት የደቡብ ወሎ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ አስያ ኢሳ ሲሆኑ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች የእራት ግብዣና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

እንኳን ደስ ያላችሁ እንኳን ደስ ያለን በቀስት ስፖርት  ደቡብ ወሎ በበላይነት አጠናቀቀ🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹በ23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር በደሴ ከተማ ሲካሄድ በሴቶች በወ...
04/03/2026

እንኳን ደስ ያላችሁ እንኳን ደስ ያለን በቀስት ስፖርት ደቡብ ወሎ በበላይነት አጠናቀቀ
🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹🏹
በ23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር በደሴ ከተማ ሲካሄድ በሴቶች በወንዶችና በድብልቅ ውድድር 3ዋንጫዎችን በማንሳት አጠናቋል።
ድሉ ይቀጥላል

23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር በደሴ ከተማ እየተካሄደ ነው
04/03/2026

23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር በደሴ ከተማ እየተካሄደ ነው

23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር 17ኛው የባህል ፌስቲቫል በደሴ ከተማ እየተካሄደ ይገኛልበሁለተኛው ቀን ውሎ ደቡብ ወሎ በበርካታ ውድድሮቾን አካሂዶ ጠንካራ ፉክክር እያደረገ ይ...
02/03/2026

23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር 17ኛው የባህል ፌስቲቫል በደሴ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
በሁለተኛው ቀን ውሎ ደቡብ ወሎ በበርካታ ውድድሮቾን አካሂዶ ጠንካራ ፉክክር እያደረገ ይገኛል
የካቲት 23/2018
ደሴ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👉👇👇👇👇👇
በምድብ ጨዋታዎች
በ12 ጉድጓድ ገበጣ በወንዶች ደብረ ብርሀንን ሲያሸንፍ በሴቶች ሽንፈትን አስተናግዷል።
በሻህ ወንዶች ደሴ ከተማን ቡብ ወንዶች ደብረ ብርሀንን በተመሳሳይ ደቡብ ወሎ ሲያሸንፍ በ18 ጉድጓድ ገበጣ ሴቶች በደብረ ብርሀን ተሸንፏል።
👉 ውድድሩ በነገው እለት ሲቀጥል በርካታ የማጣሪያና የፍጻሜ ውድድሮች ይደረጋሉ
==================
መረጃዎችን በፌስ ቡክ ለመከታተል
https://www.facebook.com/Southwollosport

በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን በማስመልከት በፊጣ ቀጠና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መካሄዱን የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ።‎‎‎አቀስታ፣ የካቲት 2...
02/03/2026

በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን በማስመልከት በፊጣ ቀጠና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መካሄዱን የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ።


‎አቀስታ፣ የካቲት 22/2018 (ለጋምቦ ኮሙኒኬሽን)

‎በለጋምቦ ወረዳ የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት "አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና ማንሰራራት" በሚል ሀሳብ በፊጣ ቀጠና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መካሄዱን አስታውቋል።

‎**********

🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑በገና ውድድር ደቡብ ወሎ አሸነፈ🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች እና ለ17ኛው የባህልና ኪነ ጥበብ ወድድር በደሴ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።ደሴ- የካቲት 22/...
01/03/2026

🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑
በገና ውድድር ደቡብ ወሎ አሸነፈ
🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑🏑
23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች እና ለ17ኛው የባህልና ኪነ ጥበብ ወድድር በደሴ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

ደሴ- የካቲት 22/2018/ደሴ ኮሙኒኬሽን / ውድድሩ "ጥበብና ስፖርት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል ከየካቲት 22-29/2018 ዓ.ም ነው የሚካሄደው።
በባህላዊ የስፖርት ውድድሮች ገና፣ ገበጣ፣ ሻህ፣ ቡብ፣ ትግል፣ ቀስት እና ኮርቦ እንደሚካሄድም ተገልፅዋል።
በእለቱ በተደረገው የመክፈቻ የገና ውድድር ሲደረግ
ደቡብ ወሎ ደሴ ከተማን 3 -0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

በባህል ስፖርቶች  እና በባህልና ኪነ ጥበብ ወድድር ዳኝነት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ፡፡ደሴ፤ የካቲት 21/2018 ዓ.ምለ23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች እና ለ17ኛው የባህልና ኪነ ጥበብ...
28/02/2026

በባህል ስፖርቶች እና በባህልና ኪነ ጥበብ ወድድር ዳኝነት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ፡፡
ደሴ፤ የካቲት 21/2018 ዓ.ም
ለ23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች እና ለ17ኛው የባህልና ኪነ ጥበብ ወድድር ከዳኝነትና ነጥብ አያያዝ ጋር በተያያዘ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በውይይቱም የዳኝነት ውሳኔ አሰጣጥ፣ ስፖርታዊ ጨዋነት ለስፖርታዊ ውጤታማነት እና መሰል ተያያዥ ጉዳዮች ተነስተዋል፡፡
በመርሃ ግበሩ የአብክመ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ም/ቢሮ ኃላፊ አየለ አናውጤ /ዶ.ር/ የተገኙ ሲሆን የውድድሩ ዓላማ በሀገር አቀፍ ለሚካሄዱ ውድድሮች ብቁ ተሳታፊዎችን ለመመልምል፣ የባህልና ኪነ ጥበብን እንዲሁም የባህል ስፖርት ዘርፍን ለማሳደግ ነው ብለዋል፡፡ ደ/ር አየለ አክለውም ውድድሩ ሲካሄድ ዳኞች ህግና ደንቡን መሰረት አድርገው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
ደሴ ከተማ በሚካሄደው ወድድር ደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣ ሰሜን ሽዋ ዞን፣ አሮሞ ብሄረሰብ ዞን፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ደሴ ከተማ አስተዳደደር፣ ሰሜን ወሎ ዞንና ወልድያ ከተማ አስተዳዳር እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡
በባህላዊ የስፖርት ውድድሮች ገና፣ ገበጣ፣ ሻህ፣ ቡብ፣ትግል: ቀስት እና ኮርቦ እንደሚካሄድም በውይይቱ ተመላክቷል፡፡
23ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድርና 17ኛው የአማራ ክልል የባህልና ኪነ ጥበብ ፌስቲቫል እሁድ የካቲት 22/2018 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሽልማት - 2017 አሸናፊዎችየኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇በወሎ ሊግ ጠንካራ አቅሙን አሳይቶ ለታላቅ ክብር የደረሰው 🌹 አንተነህ ...
25/02/2026

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሽልማት - 2017 አሸናፊዎች

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
በወሎ ሊግ ጠንካራ አቅሙን አሳይቶ ለታላቅ ክብር የደረሰው
🌹 አንተነህ አረጋ 🌹 በ2017 ከ20 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውደድርን በብቃት በመምራት ምስጉን ዳኛ በመሆን ተመርጧል
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
እንኳን ደስ ያለህ እንኳን ደስ ያለን
⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽንም በዘርፉ ኮከቦችን መርጦ እውቅና በመስጠት ሽልማት አበርክቶላቸዋል።
ኮከብ ተጫዋች - ሚኪያስ በዳሶ - ኢትዮጵያ ቡና (35,000)
ምርጥ ግብ ጠባቂ - ትንሣኤ ማርቆስ - ሲዳማ ቡና (20,000)
ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ - 13 ጎል - አንዋር ሙቀዲስ - ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ (35,000)
ኮከብ አሰልጣኝ - አምኃ ዘውዱ - ሲዳማ ቡና (30,000)
👉 ምስጉን ዳኛ - አንተነህ አረጋ (30,000)
👉 ምስጉን ረዳት ዳኛ - ሙሉ በሪሁ (20,000
በድጋሚ እንኳን ደስ ያለህ

Address

Dessie

Telephone

+251911844922

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South wollo sports posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to South wollo sports:

Share

Category