ሕብር ስፖርት Hibir Sport

ሕብር ስፖርት Hibir Sport ሕብር ስፖርት ዘወትር ረቡዕ ከ ምሽቱ 12:00-1:30 ድረስ ከሔራ ማስታወቂያ ድርጅት ጋር በመተባበር በ ኢቢሲ ኤፍኤም 104.7 ይደመጣል።

**"የፈርጉሰን ህግ፦ ስኬት የእረፍት ጊዜ አይደለም!" 🏆🔴**ብዙ አሰልጣኞች አንድ ዋንጫ ሲያነሱ ለሳምንታት በደስታ ይሰክራሉ። ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ግን የተለዩ ነበሩ። ዲሜታር ቤርባቶቭ በ...
08/02/2026

**"የፈርጉሰን ህግ፦ ስኬት የእረፍት ጊዜ አይደለም!" 🏆🔴**

ብዙ አሰልጣኞች አንድ ዋንጫ ሲያነሱ ለሳምንታት በደስታ ይሰክራሉ። ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ግን የተለዩ ነበሩ። ዲሜታር ቤርባቶቭ በቅርቡ በአንድ ፖድካስት ላይ የሰጠው ምስክርነት የዩናይትድን የአሸናፊነት ምስጢር ይገልጣል።

**ታሪኩ እንዲህ ነው፦**
በ2007/08 የውድድር ዘመን ማንችስተር ዩናይትድ ሻምፒዮን በሆነበት ወቅት፣ ተጫዋቾቹ ዋንጫውን እየተቀባበሉ ፎቶ ይነሱና ወዲያውኑ መልሰው ያስቀምጡት ነበር። ቤርባቶቭ እንደሚለው፣ ፈርጉሰን ከመጠን ያለፈ የደስታ አከባበር እንዲኖር አይፈቅዱም ነበር።

**ለምን?**
ፈርጉሰን አንድ የማይናወጥ መርህ ነበራቸው፦ **"ተጫዋቾች በስኬታቸው መደሰት ያለባቸው ጫማቸውን ከሰቀሉ በኋላ ነው።"**

**ቁምነገሩ እዚህ ጋር ነው፦**
* **ስኬት እንደ መዘናጊያ፦** ፈርጉሰን አንድ ስኬት ላይ ረክቶ መቆም ለቀጣዩ ውድቀት በር መክፈት እንደሆነ ያምኑ ነበር። ዛሬ ያሸነፍከው ዋንጫ ለነገው ድል ዋስትና አይሆንህም።
* **የረሃብ ስሜት (Hunger)፦** ተጫዋቾቻቸው ሁልጊዜም "ያልጠገቡ" እንዲሆኑ ይፈልጋሉ። አንዱን ዋንጫ እንዳነሱ፣ አእምሯቸው ወደ ቀጣዩ የውድድር ዘመን እንዲያልም ያደርጉታል።
* **ስራ እና ጡረታ፦** "ስራ ላይ ካለህ ለቀጣዩ መትጋት እንጂ ባለፈው መመካት አይገባህም" የሚለው መርሀቸው፣ ዩናይትድ ለ20 አመታት በከፍተኛ የውድድር መንፈስ ውስጥ እንዲቆይ አድርጎታል።

ፈርጉሰንን ትልቅ አሰልጣኝ ያስባላቸው፣ የእንግሊዝን ሊግ ማሸነፍ ቀላል ያስመሰሉባቸው ምስጢር ይሄው ነው፦ **ስኬትን እንደ መድረሻ ሳይሆን፣ ለቀጣዩ ስኬት እንደ መነሻ ማየታቸው!**

እግር ኳስ ብቻ ሳይሆን ህይወትም እንዲህ ናት። በአንድ ድል የምትረካ ከሆነ፣ ትልቅ ታሪክ ለመስራት እድሉን ታጣለህ።

**እናንተስ ምን ትላላችሁ? የፈርጉሰን 'አምባገነንነት' የሚመስል ጥብቅ መመሪያ ለተከታታይ ስኬት ብቸኛው መንገድ ነው?**

#ኢትዮጵያ #እግርኳስ

--

1. Sam Allardyce ስለ ፔፕ 1000 ጨዋታ📌"እንደ አሰልጣኝ 1000 ጨዋታዎች ላይ መድረስ በመቻልህ እንኳን ደስ አለህ ፔፕ። ካስታወስክ ለመጀመርያ ጊዜ የተገናኘነው 2005/06 ላይ ...
12/11/2025

1. Sam Allardyce ስለ ፔፕ 1000 ጨዋታ

📌"እንደ አሰልጣኝ 1000 ጨዋታዎች ላይ መድረስ በመቻልህ እንኳን ደስ አለህ ፔፕ። ካስታወስክ ለመጀመርያ ጊዜ የተገናኘነው 2005/06 ላይ ነበር ባርሴሎና መጥቼ ለቦልተን ወንደረርስ ላስፈርምህ ስሞክር ነበር።"

"አራት ክለቦችን በክሪስታል ፓላስ፣ ኤቨርተን፣ ሰንደርላንድ እና ዌስትብሮም ይዤ ካንተ ተጫውቼ ነበር በሚያሳዝን ሁኔታ ከእነዚህ ክለቦች ውስጥ በአንዱም ማሸነፍ አልቻልኩም ነገር ግን አንተን በማግኘቴ እና አንተን በማወቄ በጣም ደስተኛ ነኝ። ለውድድር አመቱ መልካሙን ሁሉ እመኝልሀለው።"

💙 እግር ኳስ ተመልካች ከሆንክ ይሄን ቻናል መቀላቀል አለብክ

የተጓደሉ ተጫዋቾችን ሙሉ
02/11/2025

የተጓደሉ ተጫዋቾችን ሙሉ

💥የተሳሳተ ምርጫ👉ሙድሪክ ከአርሰናል ይልቅ ቸልሲን መረጠ👉ጋክፖ ከዩናይትድ ይልቅ ሊቨርፑልን መረጠሁለቱም ከምርጫቸው እጅግ የራቀ ዓመት አሳልፈዋል።
20/05/2023

💥የተሳሳተ ምርጫ

👉ሙድሪክ ከአርሰናል ይልቅ ቸልሲን መረጠ
👉ጋክፖ ከዩናይትድ ይልቅ ሊቨርፑልን መረጠ

ሁለቱም ከምርጫቸው እጅግ የራቀ ዓመት አሳልፈዋል።

💥የ2022/23 ውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕርሚዬር ሊግ የወርቅ ጓንት ተሸላሚ በረኛ ተለይቶ ታውቋል።      ዴቪድ ዴሂያ!👏👏
20/05/2023

💥የ2022/23 ውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕርሚዬር ሊግ የወርቅ ጓንት ተሸላሚ በረኛ ተለይቶ ታውቋል።

ዴቪድ ዴሂያ!👏👏

💥የባህር ዳር ከተማ የጤና ስፖርት የእግር ኳስ ውድድር የቅዳሜና እሁድ ውጤቶች እና የደረጃ ሰንጠረዥ👉ቅዳሜ ጥር 20/2015ዓ/ም⏰ 3:00 አመስድ 2 - 1 አሚኮ⏰ 5:00 ሳይንስና ቴክኖሎጂ...
29/01/2023

💥የባህር ዳር ከተማ የጤና ስፖርት የእግር ኳስ ውድድር የቅዳሜና እሁድ ውጤቶች እና የደረጃ ሰንጠረዥ

👉ቅዳሜ ጥር 20/2015ዓ/ም

⏰ 3:00 አመስድ 2 - 1 አሚኮ
⏰ 5:00 ሳይንስና ቴክኖሎጂ 3 - 2 አውስኮድ
⏰ 8:00 አልማ 0- 0 ኢትዮ ቴሌኮም
⏰ 10:00 አግሮ ፕሮሰሲንግ 2- 7 ሰላም ካምፓስ

👉እሁድ ጥር 21/2015 ዓ/ም

⏰ 3:00 ፍትህ ማሰልጠኛ 2 - 1 ቢ አይ ካ
⏰ 5:00 አማራ ብረታብረት 1 - 2 ግሽዓባይ ካምፓስ
⏰8:00 ባ/ዳር ዙሪያ 2 - 5 ይልቃል ኤሌክትሮኒክስ
⏰10:00 ባ/ዳር ጨጨፋ 4- 0 ዓባይ ባንክ

ፌስቡክ👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100089450811611
👉ቴሌግራም https://t.me/hibirsport

በጣሊያን ሴሪ ኤ ሻምፒዮኑ ኤሲሚላን በ ሜዳው 16ኛ ደረጃ ላይ በሚገኘው ሳሱኡሎ 2-5 ተሸንፏል። ሚላን በሁሉም ውድድሮች ለተከታታይ ስድስት ጨዋታወች ማሸነፍ አልቻለም። ፌስቡክ https://...
29/01/2023

በጣሊያን ሴሪ ኤ ሻምፒዮኑ ኤሲሚላን በ ሜዳው 16ኛ ደረጃ ላይ በሚገኘው ሳሱኡሎ 2-5 ተሸንፏል።
ሚላን በሁሉም ውድድሮች ለተከታታይ ስድስት ጨዋታወች ማሸነፍ አልቻለም።

ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100089450811611
👉ቴሌግራም https://t.me/hibirsport

💥ኤቨርተን አሰልጣኝ ለመሾም ተቃርበዋል ! አሰልጣኝ ፍራንክ ላምፓርድን ያሰናበቱት ኤቨርተኖች በቀጣይ ሰዓታት አልያም በጥቂት ቀናት ውስጥ አዲስ አሰልጣኝ ለመቅጠር መቃረባቸው ተገልጿል።ኤቨርተ...
29/01/2023

💥ኤቨርተን አሰልጣኝ ለመሾም ተቃርበዋል !

አሰልጣኝ ፍራንክ ላምፓርድን ያሰናበቱት ኤቨርተኖች በቀጣይ ሰዓታት አልያም በጥቂት ቀናት ውስጥ አዲስ አሰልጣኝ ለመቅጠር መቃረባቸው ተገልጿል።

ኤቨርተኖች አሰልጣኝ ሻን ዳይክን በሁለት ዓመት ኮንትራት ቡድኑን እንዲያሰልጥን ከስምምነት መድረሳቸው ሲነገር በቅርቡ ይፋ እንደሚሆን ተዘግቧልተዘግቧል።

ቶማስ ፓርቴ ለ ኤቨርተን ጨዋታ ይደርሳል ተባለ። ጋናዊው የ መሀል ተጫዋች ቶማስ ፓርቴ በ ዘንድሮው የ አርቴታ ቡድን ውስጥ ወሳኝ ከሚባሉ ተጫዋቾች አንዱ ሲሆን ትላንት አርሰናል ከ ማንችስተር...
28/01/2023

ቶማስ ፓርቴ ለ ኤቨርተን ጨዋታ ይደርሳል ተባለ። ጋናዊው የ መሀል ተጫዋች ቶማስ ፓርቴ በ ዘንድሮው የ አርቴታ ቡድን ውስጥ ወሳኝ ከሚባሉ ተጫዋቾች አንዱ ሲሆን ትላንት አርሰናል ከ ማንችስተር ሲቲ ባደረጉት ጨዋታ መጠነኛ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወቃል። ሆኖም በተደረገለት ምርመራ ጉዳቱ ለ ክፉ የማይሰጥ እና ለቀጣዩ የመድፈኞቹ ጨዋታ እንደሚደርስ ሀኪሞች አስታውቀዋል።

ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100089450811611
👉ቴሌግራም https://t.me/hibirsport

💥የዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን ቅጣት ተጣለበት !ፊፋ የዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች በኳታሩ ዓለም ዋንጫ ወቅት ዋና ዳኛውን ያለአግባብ በማዋከባቸው ምክንያት ብሔራዊ ቡድኑ ላይ የቅጣት ውሳኔዎችን...
28/01/2023

💥የዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን ቅጣት ተጣለበት !

ፊፋ የዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች በኳታሩ ዓለም ዋንጫ ወቅት ዋና ዳኛውን ያለአግባብ በማዋከባቸው ምክንያት ብሔራዊ ቡድኑ ላይ የቅጣት ውሳኔዎችን ማስተላለለፉ ተገልጿል ።

ፊፋ ዳኛው ላይ ከፍተኛ ጫና አድርገው የነበሩትን ፈርናንዶ ሙስሌራን እና ጆዜ ማርያ ጂሚኔዝ እያንዳንዳቸው #አራት ጨዋታዎች እገዳ እና 21 ሺ ዶላር የገንዘብ ቅጣት ወስኖባቸዋል ።

በተጨማሪም ኤዲንሰን ካቫኒ እና ዲያጎ ጎዲን አንድ የብሄራዊ ቡድኑን ጨዋታ እንዲቀጡ እና 15 ሺ ዶላር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍሉ ተወስኖባቸዋል ።

እንዲሁም ሁሉም ተጨዋቾች የማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጡ ሲወሰን ብሄራዊ ቡድኑ ደግሞ አንድ ጨዋታ በዝግ ስታዲየም እንዲያደርግ እና የ54 ሺ ዶላር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል ተወስኖበታል ።

ፌስቡክ👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100089450811611
👉ቴሌግራም https://t.me/hibirsport

Address

Debra Markos

Opening Hours

18:00 - 19:30

Telephone

+251918167199

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሕብር ስፖርት Hibir Sport posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share