02/09/2018
የእሁድ 27/12/2010 ስፖርታዊ መረጃዎች
ቶሎ-ቶሎ ዜናዎችን እንድናደርሳችሁና ምንም ዜና እንዳያመልጣቹ ከታች Like ማድረግዎን አይርሱ! ከተመቻቹ ደግሞ ሼር ያርጉት።
════════════════════════
በዜናወቻችን ላይ የተካተቱትን በጥቂቱ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣
የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ የሆኑት አወዛጋቢ ሰዉ ጆዜ ሞሪኖ በክረምቱ የዝዉዉር መስኮት ላይ የ5 ጊዜ የባላንዶር አሸናፊዉን ክርስቲያኖ ሮናልዶን ከሪያል ማድሪድ ወደ
ጁቬንትስ ሳይዘዋወር በፊት ወደ ክለባቸዉ ማንችስተር ዩናይትድ የማምጣት ፍላጎት እንዳልነበራቸዉ ተገልፆ።
ተያይዞም ጆዜ ከክለቡ ጋርም ባሳለፍነዉ ክረምቱ የዝዉዉር መስኮት ላይ በዉዝግብ ምክንያት አሳልፈዋል ተብሎል።(bbc)
፡
ፈረንሳዮ አማካኝ ፖል ፖግባ በጥር ወር የዝዉዉር መስኮት ላይ ወደ ቀድሞዉ ክለቡ ጁቬንትስ የመመለስ ፈላጎት አንዳለዉ ቢነገርም ግን ፖግባ ከአሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኖ ጋር ጥሩ
ግንኙነት እንዳለዉ ተናግሮል። (sun)
:
የ26 አመቱ ብራዚላዊዉ ቄንጠኛ ተጫዋች ኔይማር ጁኔር ወደ እንግሊዞቹ ክለቦች ወደ ሆኑት አርሰናል እና ቼልሲ የመሄድ ፈላጎት አለዉ ተብሎል። ኔይማርም ለንደን ከተማ የመሄድ
ፍላጎት መኖሩን ተከትሎ ለወደፊቱ ከሁለቱ ክለቦች አንዳቸዉን ሊቀላቀል ይችላል ሲል፣ (Sunday express) ዘግቧል።
:
የቶተንሃሙ አማካኝ ቤልጀማዊዉ ሙሳ ዴንቤሌ በጥር ወደ ቻይና ሱፐር ሊግ ክለብ ወደ ሆነዉ ቤጅንግ ሲኖቦ ጁአን በ3 አመት የዉል ስምምነት፣ ሳምንታዊ ደሞዙ £192,000
በማድረግ ያመራል ተብሎል። (marca)
:
የማንችስተር ሲቲ ክለብ በለሀብት የሆኑት ሸክ መንሱር የክለባቸዉን ስታዲየም የሆነዉን ኢትሃድን ደጋፊወችን የመያዝ አቅሙን ከፍ ለማድረግ አስበዋል።(sky sport)
:
ቶተንሃሞች አይናቸዉን ከአያክሱ አማካኝ ፍራንክ ዲጆንግ ላይ አሳርፈዋል። በጥር ወደ ክለባቸዉ ለማዘዋወር ሲሉ።(mail)
:
ኮሎቢያዊዉ ተከላካይ ዮሪ ሚና በክረምቱ የዝዉዉር መስኮት ወደ ማንችስተር ዩናይትድ ሊዘዋወር ነዉ ተብሎ ሲጠበቅ ወደ የመርሳይዱ ክለብ ኤቨርተንን ተቀላቀለ። የዚህ ምክንያት
ደግሞ የኤቨርተኑ አሰልጣኝ ማርኮ ሲሊቫ ናቸዉ፣ ነገሩም ማርኮ ሲሊቫ ለዪሪ ሚና በስልክ ደዉለዉ ከማን ዩናይትድ ጋር ያለዉን የዝዉዉር ንግግር አቁሞ ወደ ክከባቸዉ ኤቨርተን
እንዲቀላቀል አነጋገሩት በዚህም ወጣቱ ተከላካይ ዩሪ ሚና አሳቡን ቀይሮ ወደ ኤቨርተን ሊቀላቀል ችሎል።(daily mirror)
:
የአርሰናሉ አሰልጣኝ ዩና ኤምሪ በፕሪሜየር ሊጉ የእረጅም እግር ኳስ አጨዋወትን ከመከተል ይልቅ አጭር የእግር አጨዋወት ፍልስፍናን ቢከተሉ የተሻለ እንደሆነ የተለያዩ
የእግር ኳስ ባለሞያወች ተናግረዋል።(star)
:
የቀድሞዉ የአርሰናል የአሁኑ የዌስታሃም ተጫዋች ጃክ ዊሊሸር በእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን በአሰልጣኝ ግሬጅ ሳዉዚጌት እንዲመረጥ ወደ ቀድሞዉ ብቃቱ መመለስ እንዳለበት ተነግሮል።(sport)