24/04/2023
በተለያዩ ከተሞች ከህዳር 20 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የአንደኛ ሊግ የምድብ ጨዋታዎች አስራ ሁለት ክለቦችን ወደ ማጠቃለያ ውድድር አሳልፎ ተጠናቋል።
የምድብ ጨዋታዎች በሚደረጉበት ወቅት ከምድብ ሀ ሙከጡሪ ከምድብ መ ደግሞ ቡሌ ሆራ እና ገደብ አሳሳ በበጀት ዕጥረት የተነሳ ውድድሩን ማቋረጣቸው የሚታወስ ሲሆን ሦስቱን ክለቦች ጨምሮ በድምሩ አስራ ሁለት ክለቦች ወደ ክልል ውድድሮች መውረድም ችለዋል።
ግንቦት 1 በአዳማ ከተማ ወደ 2016 የከፍተኛ ሊግ ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ክለቦች የሚለዩበት ውድድር የሚጀመር ሲሆን ከየምድባቸው ከአንድ እስከ ሦስት የወጡ ክለቦች በዚህ በማጠቃለያው ውድድር የሚሳተፉ ይሆናል።
በምድብ ሀ – ዱከም ከተማ ፣ ዶሬ ላንጋኖ እና አሶሳ ከተማ
ምድብ ለ – አማራ ውሀ ስራ ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና ሞጆ ከተማ
ምድብ ሐ- ሱልልታ ከተማ ፣ ጎፋ ባራንቼ እና አዲስ ቅዳም
ምድብ መ – ኦሮሚያ ፓሊስ ኮሌጅ ፣ ንፋስ ስልክ እና ሞጣ ከተማ በማጠቃለያው ውድድር የሚሳተፉ ይሆናል።
https://telegram.me/AWWCEFC
https://m.facebook.com/AWWCEFC/
Awwce Football Club, commonly referred to as አውስኮድ, is a professional football club based in Bahirda