Bahir Dar Stadium Center

Bahir Dar Stadium Center Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bahir Dar Stadium Center, Stadium, arena & sports venue, Bahir Dar.

የባህር ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታድየም ዓለም ዓቀፍ ስታንዳርድ ጠብቆ መገንባቱ ለልምድ ልውውጥ አመቺ መሆኑ ተነገረ። ታህሳስ 6/2018 ዓ.ም ከሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እንግዶች የባ/ዳር ...
16/12/2025

የባህር ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታድየም ዓለም ዓቀፍ ስታንዳርድ ጠብቆ መገንባቱ ለልምድ ልውውጥ አመቺ መሆኑ ተነገረ።
ታህሳስ 6/2018 ዓ.ም

ከሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እንግዶች የባ/ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታዲየምን ጎበኙ ።

የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃሳ አገኘሁ በጉብኝታቸው በሲዳማ ክልል በአዋሳ ከተማ የተጀመረውን ዓለም ዓቀፍ ስታድየም ግንባታ ለማስቀጠል የባህር ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታዲየምን መጎብኘት አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ተናግረው ጉብኝታቸው ሰፊ ልምድና ተሞክሮን ለመቅሰም እንዳስቻላቸው ገልፀዋል።

የባህር ዳር አለም አቀፍ ስታዲየም በጣም ጥቃቅን የፊኒሽንግ ስራዎች ቢኖሩትም በካፍ እና ፊፋ ዓለም ዓቀፍ ስታንዳርድ የተገነባ እጅግ ውብ ስታድም ነው ሲሉም አቶ ጃሳ ተናግረዋል ።

የስፖርት ልማቱ ልፋትና ጥረትም ውጤታማ የሆኑ ሀገርን የሚያስጠሩ እንዲሁም የሚጠቅሙ ስፖርተኞችን ለማልማት ነውም ብለዋል።

ካሱ አሩሳ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ በበኩላቸው በጉብኝታቸው ወቅት በርካታ ጠቃሚ ልምዶችን እንደቀሰሙ ተናግረው በሀገር አቀፍ ደረጃ የስፖርቱን ዘርፍ ለማሳደግ በመንግስት በኩል በስፋት ታቅዶበት እየተሰራ እንደሆነ አስታውሰው ለዚህም የስፖርቱን ዘርፍ ልማት ማልማት ቀዳሚ ተግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል ።

የአብክመ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋየ እንደተናገሩት ከሲዳማ ክልል የመጡት እንግዶች ጉዞ ዋና ዓላማ የአዋሳን ዓለም ዓቀፍ ስታድየም ለመገንባት የሚጠቅሙ ልምዶችን ለመቅሰም ከመሆኑም ባሻገር የእርስ በርስ ግንኙነትን ለማጠናከር የሚጠቅም እንደሆነ ተናግረዋል ።

የባህር ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታድየም መጠናቀቁ ከዛሬው የልምድ ልውውጥ ጀምሮ በርካታ የስፖርት ቱሪዝም እንቅስቃሴ እንዲኖር ከማድረጉም በላይ ለባህር ዳር ከተማ ሰፊ የኢኮኖሚ መነቃቃትን የሚያድል ተቋም እንደሆነ ኃላፊው አክለው ገልፀዋል።

የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የከተማዋን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ለማነቃቃት ሚናው የጎላ ነው።ኅዳር 17/2018 ዓ.ምበባሕር ዳር ከተማ እየተገነቡ ካሉት ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል የባሕር ዳ...
26/11/2025

የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የከተማዋን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ለማነቃቃት ሚናው የጎላ ነው።
ኅዳር 17/2018 ዓ.ም

በባሕር ዳር ከተማ እየተገነቡ ካሉት ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም አንዱ ነው። ከተማዋ በአሁኑ ወቅት እያከናወነችው ካለው የኮሪደር ልማት ጋር ተዳምሮ አዲስ ገጽታን እየፈጠረ ነው።

ስታዲየሙ የከተማዋን ብሎም የክልሉን ገጽታ በመገንባት የቱሪዝሙን እንቅስቃሴ ከፍ ለማድረግ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበታል።

ስታዲየሙ በርካታ ዓመታትን በግንባታ አሳልፎ አሁን ላይ ወደ መጠናቀቁ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ወንበሮች እየተገጠሙለት፣ የገጸ ምድር ማሥዋብ እና የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተሠሩለት ነው። ይህንን ተከትሎ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ስታዲየሙን እየጎበኙት ይገኛሉ።

አሚኮ ያነጋገራቸው ከአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር የመጡት በዕውቀት ገዛኸኝ የባሕር ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታዲየም ግንባታ መጠናቀቅ የምንናፍቀውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እንደ አንድ መሥፈርት ስለሚወሰድ ሚናው ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

ቱሪዝም አንድ አዋጭ የኢኮኖሚ ዘርፍ ተደርጎ መያዙን ጠቁመው ስታዲየሙ ለቱሪዝም ዕድገት ድርሻው የጎላ ስለመኾኑ አንስተዋል። በተለይም ስፖርት ቱሪዝም በአንድ ጊዜ ብዙ አካላትን የሚያንቀሳቅስ በመኾኑ ለክልሉ የስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ነው የገለጹት።

ከሰሜን ወሎ ዞን እንደመጡ የነገሩን ፈንታው በለጠ በበኩላቸው ስታዲዬሙ ከክልሉ አልፎ ሀገር አቀፍ ስፖርትን የሚያነቃቃ ስለመኾኑ ጠቁመዋል። ዓለም አቀፍ የስፖርት ዝግጅቶችንም ለማዘጋጀት አቅም የሚኾን እንደኾነም ነው የገለጹት።

የባሕር ዳር ከተማን የቱሪዝም እንቅስቃሴ የሚያነቃቃ እና ገጽታዋን የሚያጎላም ነው ብለዋል። ትልቅ የሀገር ሃብት በመኾኑ ሙሉ በሙሉ እንዲጠናቀቅ መንግሥት ከወሰደው ቁርጠኝነት በተጨማሪ መላውን ሕዝብ መደገፍ እንደሚገባውም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ በላይነሽ ሲሳይ ስታዲየሙ ከስፖርታዊ ጠቀሜታው ባለፈ በክልሉ ለቱሪዝም ዘርፍ ተስፋ ከተጣለባቸው ጸጋዎች መካከል አንዱ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በ2029 ለማዘጋጀት ጥያቄ ላቀረበችው የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ኹኔታዎችን ለማሟላም ሚናው ከፍ ያለ መኾኑን አስረድተዋል።
አሚኮ

የባሕር ዳር ስታዲየም ለባሕር ዳር ከተማ ተጨማሪ ውበት ነው።ኅዳር 17/2018 ዓ.ምየአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች የባሕር ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታዲየምን እየጎበኙ ነው።በጉብኝቱ እ...
26/11/2025

የባሕር ዳር ስታዲየም ለባሕር ዳር ከተማ ተጨማሪ ውበት ነው።
ኅዳር 17/2018 ዓ.ም

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች የባሕር ዳር ዓለም ዓቀፍ ስታዲየምን እየጎበኙ ነው።

በጉብኝቱ እየተሳተፉ አሚኮ ያገኛቸው አቶ ፈንታው በለጠ ስታዲየሙ በችግር ሳይቆም በዚህ ደረጃ ተገንብቶ በማየታቸው መደነቃቸውን ገልጸዋል። ትልቅ ኩራት እንደተሰማቸውም አስረድተዋል። ስታዲየሙ የሀገር አቀፍ ትኩረትን የሚስብ እና ለስፖርት ቱሪዝሙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።

ስታዲየሙ ለባሕር ዳር ከተማ ተጨማሪ ውበት መኾኑንም ነው የተናገሩት። የከተማዋን ብሎም የክልሉን እንቅስቃሴ የሚያነቃቃ ተጨማሪ አቅም ስለመኾኑም አመላክተዋል። ስታዲየሙ ተደጋግሞ ቢጎበኝም የማይጠገብ ነው ብለዋል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ በላይነሽ ሲሳይ ስተዲየሙ ለቱሪዝም ዘርፉ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ እንደኾነ ጠቁመዋል። ለኢኮኖሚው ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ነው የተናገሩት።

የስታዲየሙ መጠናቀቅ በክልሉ የተጀመረውን ልማት ለማስቀጠል ትልቅ ማሳያ ስለመኾኑም ነው ያነሱት።
አሚኮ

18/11/2025
08/11/2025
08/10/2025

የባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም አስደናቂ ገፅታን ፈጥሯል፤ ለጨዋታም ዝግጁ እየሆነ ይገኛል። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ
የስታዲየሙ ሜዳ የተተከለለት ሳር ለዓለም አቀፍ የእግርኳስ ጨዋታዎች ምቹና ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን ከአማራ ክልል እና የባህር ዳር ከተማ አመራሮች ጋር ባደረግነው የሙከራ የኳስ ጨዋታ ተመልክተናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍቅርና የስኬት ይሁንልን፡፡ አቶ እርዚቅ ኢሳየባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ እርዚቅ ኢሳ  አዲሱን ዓመት አስመልክቶ የመልካም ...
10/09/2025

አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍቅርና የስኬት ይሁንልን፡፡
አቶ እርዚቅ ኢሳ

የባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ እርዚቅ ኢሳ አዲሱን ዓመት አስመልክቶ የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

አዲሱ ዓመት 2018 በርግጥም የኩስመና ታሪካችን ተቀይሮ የማንሰራራት ዓመት ይሆናል ብለዋል፡፡ የክልላችን መንግስት ከግጭትና ድህነት አዙሪት በመውጣት ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል የ25 ዓመት አሻጋሪ እቅድ በማዘጋጀት ወደ ስራ ገብቷል ያሉ ሲሆን ይህ እቅድ የክልላችን ወጣቶችን ሁነኛ የልማት አቅም በማድረግ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት የማረጋገጥ ህልም ይዞ የተነሳ በመሆኑ ለስኬታማነቱ ወጣቶች በባለቤትነት ሊሳተፉበት ይገባል በማለት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በስፖርቱ ዘርፍ ጤናው የተጠበቀና ለሀገር የሚጠቅም ብቁ ዜጋ ለማፍራት የሚያስችሉ የስፖርት መሰረተ ልማቶችን በሟማለት ረገድ ተስፋ ሰጭ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በዚህ ረገድ የክልሉ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲምን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ የክልላችን ብሎም የሀገራችን ወጣቶች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አቅዶ እየሰራ ነው፡፡ በአዲሱ ዓመት 2018 ዓ.ም አጋማሽም ግንባታውን በማጠናቀቅ በጉጉት ለሚጠብቀው የሀገራችን ህዝብ ክፍት ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ቦርድ ሰብሳቢው አክለው ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም በአዲሱ ዓመት የክልላችን ወጣቶች ሰላማችን ለማረጋገጥ እና ከግጭትና ከድህነት አዙሪት ለመውጣት የሚደረገው ጥረት መሪ ተዋናኝ በመሆን በህብር ወደ ክብር የምንጓዝበት ዓመት ይሁን ሱሉ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

በህብር ወደ ክብር፤

ለማንሰራራት እንተጋለን፤

ለሰላምና ለሀገራዊ ህብረት በጋራ እንተማለን፤

መጨው አዲስ ዓመት 2018 የሰላም፣ የፍቅርና የስኬት እንዲሆንልን እመኛለሁ፡፡

ጳጉሜን ሁለት  "የኅብር ቀን" በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታድየም በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው። ጳጉሜን ሁለት  "የኅብር ቀን"ን ምክንያት በማድረግ የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎ...
07/09/2025

ጳጉሜን ሁለት "የኅብር ቀን" በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታድየም በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።

ጳጉሜን ሁለት "የኅብር ቀን"ን ምክንያት በማድረግ የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታድየም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እና የጉብኝት መርሐ ግብር እያካሄዱ ነው።

‎በመርሐ ግብሩ ላይ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኀላፊ
ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር)ን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

አሚኮ በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል ውስጥ የስፖርት ስቱዲዮ እንዲኖረው የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ። ነሐሴ 30/2017 ዓ.ምአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስ...
05/09/2025

አሚኮ በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል ውስጥ የስፖርት ስቱዲዮ እንዲኖረው የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።
ነሐሴ 30/2017 ዓ.ም

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል ጋር የስፖርት ስቱዲዮ እንዲኖረው የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል።

የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እርዚቅ ኢሳ ባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል ከአሚኮ ጋር ያደረገው ስምምነት በጋራ በመስራት የስፖርት ዘርፉን ትርጉም ባለው መልኩ ለማሳደግ ይጠቅማል ብለዋል።

ስታዲየሙ የሚጠበቅበትን ሁሉ መመዘኛ አሟልቷል ያሉት ቦርድ ሰብሳቢው አሚኮ የሚገነባው ዘመናዊ ስቱዲዮም የስታዲየሙን ደረጃ ከፍ ከሚያደርጉ እና ተመራጭነቱን ከሚጨምሩ ግብዓቶች ውስጥ አንዱ ነው ብለዋል።

ስታዲየሙ ስፖርታዊ ውድድሮችን ብቻ ሳይሆን ልዩ ልዩ ክልል አቀፍ እና ሀገራዊ ፌስቲቫሎችንም እንደሚያስተናግድ ገልጸዋል። የአሚኮ ስቱዲዮ ሁነቶችን በቅርበት ለመዘገብ ያስችላል ነው ያሉት።

ዛሬ የተደረገው የስምምነት ፊርማ በተሻለ ትብብር በመስራት ጥራት እና ቅልጥፍና ያለው አገልግሎት ለመስጠት ያግዛል ብለዋል።

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ጋዜጠኛ ሙሉቀን ሰጥዬ የአሚኮ ስፖርት ክፍል እና ባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ዓላማቸው ተመሳሳይ ነው ብለዋል። የክልሉን ስፖርት እና ስፖርተኞች እንቅስቃሴ ማሳደግ እና በክልሉ ሁለንተናዊ የዘርፉ እድገት እንዲመጣ እንደሚሰሩም ገልጸዋል።

ሁለቱም ተቋማት የበለጠ ተቀራርበው እና በጋራ በመስራት በዘርፉ ውጤታማ የሆነ ውጤት ለማስመዝገብ እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል። የዛሬው የስምምነት ፊርማም ይህንን ትብብር ለማላቅ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ ስታዲየሙ ደረጃውን ጠብቆ እንዲገነባ እና ከዚህ እንዲደርስ ሲሳተፉ የነበሩ ባለድርሻ አካላት ምስጋና ይገባቸዋል ያሉት ጋዜጠኛ ሙሉቀን አሚኮም በስታዲየሙ ውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ስቱዲዮ እየገነባ ነው ብለዋል። ይህ ዘመናዊ ስቱዲዮ መገንባቱ የስፖርት ቤተሰቦችን በቅርበት በማግኘት ውጤታማ ዘገባዎችን ለማዘጋጀት ያግዛል ነው ያሉት።

የአሚኮ መሪዎች የተሰጠውን ዕድል እና ኀላፊነት በአግባቡ በመወጣት የስቱዲዮ ግንባታውን በጥራት እና በፍጥነት እያከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል፣ የአሚኮና የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከፍተኛ መሪዎች እና የስፖርት ዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

17/08/2025
በባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል የሚገኘው ደረጃውን የጠበቀ ጅምና ፊትነስ ሴንተር።
10/08/2025

በባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል የሚገኘው ደረጃውን የጠበቀ ጅምና ፊትነስ ሴንተር።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahir Dar Stadium Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share