Bahirdar City Foot Ball Referees & Commissioners Association

Bahirdar City Foot Ball Referees & Commissioners Association ይህ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የእግር ኳስ ዳኞችና ታዛቢዎች ሙያ ማህበር ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ነው። Our game Is Fair Play

💥ለረዳት ዳኞች የባንዲራ አጠቃቀም (Flag technique) (ክፍል ሁለት)❹ በፍ/ቅ/ምት ክልል ውስጥ የተሰራ ጥፋትን ለማመልከትጥፋቱ የተሰራው በፍ/ቅ/ምት ክልል ውስጥ በተከላካይ ቡድን ከ...
31/03/2026

💥ለረዳት ዳኞች የባንዲራ አጠቃቀም (Flag technique) (ክፍል ሁለት)

❹ በፍ/ቅ/ምት ክልል ውስጥ የተሰራ ጥፋትን ለማመልከት

ጥፋቱ የተሰራው በፍ/ቅ/ምት ክልል ውስጥ በተከላካይ ቡድን ከሆነ በተለይ ደግሞ ከዳኛው እይታ ውጭ ከሆነ ባንዲራን በማንሳት ከዳኛው ጋር የአይን ለአይን ግንኙነት በማድረግ ወደ ውስጥ [ወደ ግብ መስመርና ፍ/ቅ/ምት ክልል መገናኛ] መሮጥ ያስፈልጋል።

❺ ከፍ/ቅ/ምት ክልል ውጭ የተሰራ ጥፋትን ለማመልከት

ጥፋቱ የተሰራው ከፍ/ቅ/ምት ክልል ውጭ በተከላካይ ቡድን ከሆነ በተለይ ደግሞ ከዳኛው እይታ ውጭ ከሆነ ባንዲራን በማንሳት ከዳኛው ጋር የአይን ለአይን ግንኙነት በማድረግ አንድ እርምጃ ወደ ግራ [ወደ Halfway line] በመንቀሳቀስ ማመልከት ያስፈልጋል።
በተለይ ጥፋቱ የተፈፀመው በመልሶ ማጥቃት [Counter attack] ከሆነ የጥፋቱን መጠንና በዲሲፕሊን ምን ሊያስቀጣ እንደሚችል ጭምር ለዳኛው መረጃውን በትክክል መስጠት ይጠበቅበታል።

❻ ግብ ነው/አይደለም

ግቡ የተቆጠረው በግልፅ ከሆነ ረዳት ዳኛው ከዳኛው ጋር የአይን ለአይን ግንኙነት ማድረግ ብቻ በቂ ስለሆነ ምንም አይነት ተጨማሪ ምልክት ማሳየት አያስፈልግም።

ግቡ የተቆጠረበት መንገድ ግልፅ ካልሆነ ረዳት ዳኛው ባንዲራውን በማንሳት የዳኛውን ትኩረት በመሳብ የአይን ለአይን ግንኙነት ከፈጠረ በኋላ ግቡን ማፅደቅ አለበት።

❼ ከጨዋታ ውጭ (Offside)

ረዳት ዳኛው ከጨዋታ ውጭ አቋቋም ላይ የተገኘ ተጨዋች የሚቀጣ ሲሆን ባንዲራውን ማንሳት አለበት፣ ዳኛው ከምልክቱ በኋላ ጨዋታውን ሲያቆም የሚቀጣበት ቦታ የት [ሩቅ፣ መሀል ወይም ቅርብ] መሆኑን ያመለክታል።

❽ ፍፁም ቅጣት ምት (Penalty kick)

በፍፁም ቅጣት ምት ጊዜ ግብ ጠባቂው በህግ 14 የተቀመጡትን ህጎች ጥሶ ከተገኘ ረዳት ዳኛው ባንዲራውን ማንሳት አለበት። በቅድመ ስበሰባ (Pre match meeting) በተነጋገሩት ምልክት መሰረት የጥፋቱን ሁኔታ ለዳኛው ያሳውቃል።

❾ የተጨዋች ቅያሪ (Substitution)

የተጨዋች ቅያሪ መኖሩን ከ4ኛ ዳኛው ወይም ከሌሎች የጨዋታ አመራሮች እንደተነገረው ኳስ ከጨዋታ ውጭ ስትሆን የተፈቀደለትን የተጨዋች ቅያሪ ምልክት ማሳየት አለበት።

➓ የመልስ ውርወራ (Throw-in)

ኳስ ሙሉ በሙሉ የጎን መስመሩን ለቃ ስትወጣ
👉ለረዳት ዳኛው ቅርብ በሆነው የሜዳ ክፍል በኩል ከወጣች ለየትኛው ቡድን እንደሚሰጥ ማመልከት
👉ለረዳት ዳኛው ሩቅ በሆነው የሜዳ ክፍል በኩል በግልፅ ከወጣች በቀጥታ ማመልከት ነገር ግን ጥርጣሬ ካለ ከዳኛው ጋር የአይን ለአይን ግንኙነት በመፍጠር ዳኛውን መከተል

👉በመጨረሻም

ረዳት ዳኞች በህግ የተቀመጠ ግልፅ የሆነ የእጅ ምልክት ስለሌላቸው የእጅ ምልክት መጠቀም የለባቸውም። ነገር ግን በቅድመ ጨዋታ ስብሰባ ከዳኛው ጋር የተግባቡበት ልዩ ምልክት ካለ በተግባቦታቸው ልክ ዳኛውን ሊረዱት ይችላሉ።

💥ለረዳት ዳኞች (ክፍል አንድ)የባንዲራ አጠቃቀም (Flag technique)የረዳት ዳኞች ባንዲራ ሁሌም ያልተሸፈነና ለዳኛው እይታ ግልፅ በመሆነ መንገድ እንዲሁም ለዳኛው ቅርብ በሆነው እጅ መ...
30/03/2026

💥ለረዳት ዳኞች (ክፍል አንድ)

የባንዲራ አጠቃቀም (Flag technique)

የረዳት ዳኞች ባንዲራ ሁሌም ያልተሸፈነና ለዳኛው እይታ ግልፅ በመሆነ መንገድ እንዲሁም ለዳኛው ቅርብ በሆነው እጅ መያዝ አለበት።

✔️ ረዳት ዳኞች ማንኛውንም ምልክት ለማሳየት በቅድሚያ
👉 ሩጫን ማቆም
👉 እይታን ሙሉ በሙሉ ወደ ጨዋታው ሜዳ ማድረግ
👉 ከዳኛው ጋር የአይን ለአይን ግንኙነት (Eye contact) ማድረግ አለባቸው።

✔️ ባንዲራ እንደተራዘመ እጅ የሚቆጠር ሲሆን ረዳት ዳኞች ባንዲራ ማውጣት ያለባቸው ለቀጣይ ውሳኔ በሚመቻቸው እጅ መሆን አለበት። ነገር ግን የግድ መቀየር ካስፈለገ የባንዲራው ቅይይር ከወገብ በታች መሆን አለበት።

➡️ለመሆኑ ረዳት ዳኞች ባንዲራቸውን የሚጠቀሙት ለምን ለምን ውሳኔ ነው?

❶ ኳስ ከጨዋታ ውጭ መሆኗን ለማመልከት

👉 ረዳት ዳኛው በቅድሚያ ባንዲራውን በማንሳት ከዳኛው እውቅና ማግኘቱን ካረጋገጠ በኋላ የመልስ ምት፣ የማዕዘን ምት ወይም የመልስ ውርወራ ለየትኛው ቡድን እንደሆነ ያመለክታል።

❷ የመልስ ምት/የማዕዘን ምት ለማመልከት

ኳስ ሙሉ በሙሉ የጨዋታውን ሜዳ በግብ መስመሩ ለቃ ስትወጣ ባንዲራን በቀኝ እጅ በማንሳት (Better line of vission ግድ ነው)
👉ለረዳት ዳኛው በሚቀርብ ቦታ ከሆነ የመልስ ምት ወይም የማዕዘን ምት መሆኑን ማመልከት. . .
👉ለረዳት ዳኛው ሩቅ ባለው ቦታ ከሆነ ከዳኛው ጋር የአይን ለአይን ግንኙነት (eye contact) መፍጠርና የዳኛውን ውሳኔ መከተል. . .

ነገር ግን ኳስ የጨዋታውን ሜዳ ለቃ የወጣችው በግልፅ ከሆነ ባንዲራ ወደ ላይ ማንሳት አያስፈልግም።

❸ ጥፋቶችን ለማመልከት

ረዳት ዳኞች በአቅራቢያቸው ጥፋት ሲፈፀም ወይም ያልተገባ ባህሪይ ከተመለከቱ ባንዲራቸውን ማንሳት አለባቸው። ነገር ግን ምልክት ከማሳየታቸው በፊት ታሳቢ ማድረግ ያለባቸው ጉዳዮች አሉ።
👉ጥፋቱ የተፈፀመው ከዳኛው እይታ ውጭ መሆኑን ወይም ዳኛው በተጨዋቾች የተከለለ መሆኑን
👉ዳኛው ጥፋት ከተሰራበት ቦታ ያለውን ርቀት
👉ዳኛው የተጠቃሚነት መብትን ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን አማራጭ ታሳቢ ማድረግ ያስፈልጋል።

ረዳት ዳኛው ጥፋት ተፈፅሟል ብሎ ካሰበ ባንዲራውን ማውጣት ያለበት ለቀጣይ ውሳኔ በሚመቸው እጁ መሆን አለበት፣ ይህም ዳኛው ጥፋቱ በየትኛው ቡድን እንደተወሰነና ቅጣት ምቱን ለየትኛው ቡድን መስጠት እንዳለበት ፍንጭ ሊሰጠው ይችላል።

ከዳኛው ጋር የአይን ለአይን ግንኙነት ማድረግ እና ባንዲራን በማርገብገብ (slight Wave Back and forth) ማመልከት

ረዳት ዳኞች ጥፋት ተሰርቷል ብለው ምልክት ከማሳየታቸው በፊት "Wait and see technique"መጠቀም አለባቸው።
ይህም ጥፋት የተሰራበት ቡድን ከቅጣት ምቱ ይልቅ በተሻለ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉበት እድል ይሰጣል።

ክፍል ሁለት ይቀጥላል. . . . .

💥FIFA በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ተግባራዊ የሚያደርገው አዲሱ ህግአንድ ቡድን የተሰጠውን የመልስ ምት በ5 ሰከንድ ውስጥ ካልመታ ለተጋጣሚው ቡድን የማዕዘን ምት ይሰጣል።የዚህ ህግ ጥቅሙ ምን...
29/03/2026

💥FIFA በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ተግባራዊ የሚያደርገው አዲሱ ህግ

አንድ ቡድን የተሰጠውን የመልስ ምት በ5 ሰከንድ ውስጥ ካልመታ ለተጋጣሚው ቡድን የማዕዘን ምት ይሰጣል።

የዚህ ህግ ጥቅሙ ምንድን ነው?

◍ የሰዓት መባከንን ያስቀራል።

◍ የጨዋታውን ፍጥነት ይጨምራል።

👉አፈጻጸም

ጨዋታው የተሻለ ፍሰት እንዲኖረው ዳኞች ይህንን ህግ በማስፈጸም ለተጋጣሚው ቡድን የማዕዘን ምት ይሰጣሉ።

💥በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የባህር ዳር ከተማ ጤና ስፖርት ውድድር ቅዳሜ እና እሁድ በሚካሄዱ ጨዋታዎች ይመለሳል።👉 ቅዳሜ መጋቢት 05/2018 ዓ.ም የሚካሄዱ ጨዋታዎች  ⏰ 2፡00 ...
11/03/2026

💥በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የባህር ዳር ከተማ ጤና ስፖርት ውድድር ቅዳሜ እና እሁድ በሚካሄዱ ጨዋታዎች ይመለሳል።

👉 ቅዳሜ መጋቢት 05/2018 ዓ.ም የሚካሄዱ ጨዋታዎች



⏰ 2፡00 ኢኖቬሽን ቴክ/ጂ 🆚 ጉምሩክ ኮሚሽን

⏰ 3፡30 ጥበበ ግዮን 🆚 ሙሉቀን የመ/ኪራይ

⏰ 5:00 ንግድና ኢን/ሪ 🆚 ክልል ምክር ቤት

⏰ 8፡30 ትራንስፖርትና ሎጅ/ክ 🆚 አየር መንገድ

⏰ 10፡00 አማራ ብረታ ብረት 🆚 ኢትዮ. ቴሌኮም

👉እሁድ መጋቢት 06/2018 ዓ.ም የሚካሄዱ ጨዋታዎች

#ምድብ-ሀ

⏰ 2፡00 አቡነ ጎርጎርዮስ 🆚 ባ/ዳር ፖሊ ቴክኒክ

⏰ 3፡30 አቢሲንያ ባንክ 🆚 ገጠር መንገድ

⏰ 5:00 ባ/ዳር ጨ. ጨ. ፋ 🆚 ፍትህና ህግ ምርምር

⏰ 8፡30 አዋሽ ባንክ 🆚 ኢትዮ. ኤሌክትሪክ

⏰ 10፡00 ቢ. አይ. ቲ 🆚 ገቢዎች ሚኒስትር

🏟 አጼ ቴዎድሮስ ስታድዬም

💥ተግባራዊ መመርያዎች፤ ለግጥሚያ አመራሮች ✔️ ጨዋታ እንደገና እንዳይጀመር በማዘግየት እና ጨዋታ እንደገና ሲጀመር ተገቢውን ርቀት ባለመጠበቅ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው ?☞ዳኛው የሚከተ...
06/03/2026

💥ተግባራዊ መመርያዎች፤ ለግጥሚያ አመራሮች

✔️ ጨዋታ እንደገና እንዳይጀመር በማዘግየት እና ጨዋታ እንደገና ሲጀመር ተገቢውን ርቀት ባለመጠበቅ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው ?

☞ዳኛው የሚከተሉት ሁለት ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የማስጠንቀቂያ ካርድ ሊሰጥ ይችላል።

❶ ጨዋታ እንደገና እንዳይጀመር በማዘግየት
❷ ጨዋታ እንደገና በቅጣት ምት፣ በመልስ ምት፣ በማዕዘን ምት አልያም በመጣል ሲጀመር ተገቢውን ርቀት ባለመጠበቅ ...

✔️ ለመሆኑ በሁለቱ ጥፋቶች መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው ?

➡️ የመጀመሪያው ጥፋት, በአጥቂው ቡድን(ኳስን በተቆጣጠረው) ወይም በተጋጣሚው ሊፈፀም ይችላል። በዚህ ሁኔታ በአብዛኛው ከሚስተዋሉ ጥፋቶች መካከል፦

👉 የመልስ ውርወራ፣ የመልስ ምት እና መሰል ጨዋታን እንደገና የማስጀመርያ መንገዶች ወቅት ሆነ ብሎ ጨዋታን እንዳይጀመር ማዘግየት...

👉 በቅያሪ ወቅት የጨዋታ ሜዳ ለቆ ለመውጣት ማዘግየት...

👉 ኳስ በመያዝ/በመምታት እና ተጋጣሚ ጨዋታን እንደገና በሚጀምርበት ወቅት ተገቢ ባልሆነ መንገድ ጨዋታ እንዳይጀመር ማዘግየት...ወዘተ ይገኙበታል።

➡️ ሁለተኛው ጥፋት ወይም ተገቢውን የርቀት መጠን አለመጠበቅ/አለማክበር ማለት ፦

👉 ኳስ በመጣል በሚጀምርበት ጊዜ ለሁለቱም ቡድን ተጨዋቾች ከኳስ ቢያንስ 4 ሜትር ...

👉 በቅጣት ምት ወቅት በተከላካዩ ቡድን የግብ መስመር ላይ እና በግብ ቋሚዎቹ መሀል እስካልሆነ ድረስ 9.15 ሜትር ...

👉 የመልስ ውርወራ ከሚወረወርበት ቦታ ቢያንስ 2 ሜትር...

👉 ከማዕዘን ምት መምቻ ቅስት 9.15 ሜትር ... ርቆ አለመገኘት ማለት ነው።

ይህ ሁኔታ ጨዋታው እንደገና ከተጀመረ በኋላ ሊሆንም ይችላል።
ለምሳሌ፦ በቅጣት ምት ጊዜ ምቱ ከመመታቱ በፊት ወደፊት ሮጦ መጠጋት እና ምቱን ማቋረጥ. . . .

አንዳንድ ክስተቶች ከላይ በተገለፁት ሁነቶች ላይካተቱ የሚችልበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል። ይህ ሁኔታ ሲያጋጥም ዳኛው በይበልጥ ተገቢ በሆነው መያዝ እና ከጨዋታ በኋላ በሪፖርቱ መግለፅ ይኖርበታል።

ሼርርርርርርርርርር

💥የማህበራችን አባላት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን  ያዘጋጀውን የአካል ብቃት ፈተና በስኬት አጠናቀዋል።እንኳን ደስ አላችሁ
27/02/2026

💥የማህበራችን አባላት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያዘጋጀውን የአካል ብቃት ፈተና በስኬት አጠናቀዋል።

እንኳን ደስ አላችሁ

💥Road 2028 በባህር ዳር ተጀምሯል።ከ44 በላይ የከተማችን የፕሮጀክት ቡድኖች በተለያየ የእድሜ ደረጃ የሚያካሂዱት የምዘና ውድድር ዛሬ በድምቀት ተጀምሯል።የአማራ ክልል ባህል ቱሪዝም ስፐ...
21/02/2026

💥Road 2028 በባህር ዳር ተጀምሯል።

ከ44 በላይ የከተማችን የፕሮጀክት ቡድኖች በተለያየ የእድሜ ደረጃ የሚያካሂዱት የምዘና ውድድር ዛሬ በድምቀት ተጀምሯል።

የአማራ ክልል ባህል ቱሪዝም ስፐርት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ጋሻው ተቀባ እና የባህዳር ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ እንዲሁም ሌሎች አመራሮች ውድድሩን አስጀምረዋል።

ውድድሩ ለቀጣይ ስድስት ወራት በባህር ዳር አፄ ቴዎድሮስ ስታድየም የሚካሄድ ይሆናል።

💥የማህበራችን አባላት ዛሬ የተካሄደውን የአካል ብቃት ፈተና በብቃት አጠናቀዋል።👉ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ አማን ሞላ እና ፌደራል ረዳት ዳኛ እያሱ ካሳሁን ዛሬ የካቲት 11/2018  ዓ/ም ለ...
18/02/2026

💥የማህበራችን አባላት ዛሬ የተካሄደውን የአካል ብቃት ፈተና በብቃት አጠናቀዋል።

👉ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ አማን ሞላ እና ፌደራል ረዳት ዳኛ እያሱ ካሳሁን ዛሬ የካቲት 11/2018 ዓ/ም ለፕሪምየር ሊግ የጨዋታ አመራሮች የተሰጠውን የአካል ብቃት ፈተና በብቃት በማጠናቀቅ ለቀጣይ ስራ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ማህበራችን ለሁለቱም አባሎቻችን መልካም የጨዋታ ጊዜ ይመኛል።

💥የማህበሩ አባላት በመደበኛ ልምምድ ላይ. . .
14/02/2026

💥የማህበሩ አባላት በመደበኛ ልምምድ ላይ. . .

💥ማህበራችን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው እለት የማህበሩ አባላት በተገኙበት አካሄዷል።በስብሰባውም የማህበሩን የ2017 ዓ/ም የስራ አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ መከናወን ስላለባቸው መሰ...
13/02/2026

💥ማህበራችን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው እለት የማህበሩ አባላት በተገኙበት አካሄዷል።

በስብሰባውም የማህበሩን የ2017 ዓ/ም የስራ አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ መከናወን ስላለባቸው መሰረታዊ ጉዳዮችም ውይይት ያደረገ ሲሆን በተለያየ ምክንያት የተጓደሉ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ምርጫ አካሂዷል።

በተጨማሪም የማህበራችን አባላት ከሀገር ውስጥ የስፖርት ትጥቅ አምራች ከሆነው ዋናው ስፖርት ያሰሩትን የልምምድ ማሊያም ተረክበዋል።

የባህርዳር ከተማ መለያ በሆነው ነጭና እና ውሀ ሰማያዊ ቀለም በራሳችን የዲዛይን ምርጫ ያዘጋጀልን ዋናው ስፖርትን ከልብ እናመሰግናለን።

💥መልካም ዜና ለእግር ኳስ ዳኝነት ስልጠና ፈላጊዎች. . . .  የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝም ስፖርት መምሪያ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጋር በመተባበር ተተኪ የእግር ኳስ ...
04/02/2026

💥መልካም ዜና ለእግር ኳስ ዳኝነት ስልጠና ፈላጊዎች. . . .


የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝም ስፖርት መምሪያ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጋር በመተባበር ተተኪ የእግር ኳስ ዳኞችን ለማሰልጠን በዝግጅት ላይ ይገኛል።

በመሆኑም እድሜያችሁ ከ22 ዓመት በታች የሆናችሁና የ8ኛ ክፍል ካርድ ማቅረብ የምትችሉ እንዲሁም በእግር ኳስ ተጨዋችነት በፕሮጀክት ያለፋችሁ ተተኪዎች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

👉የምዝገባ ቦታ:- በሁሉም ክፍለ ከተሞች ከሚገኙ የስፖርት ባለሙያዎች ጋር መመዝገብ ትችላላችሁ።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር
0918090839
0918719557
0918338978 መደወል ትችላላችሁ።

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ይደረግ

💥የባህር ዳር አለም አቀፍ ስታድየም የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን እንዲያዘጋጅ ተጠየቀለሀገራችን የእግር ኳስ ዕድገት ዋነኛ እንቅፋቶች ውስጥ አንዱ የሆነው ደረጃውን የጠበቀ ሜዳ አለመኖር ሲሆን ...
28/01/2026

💥የባህር ዳር አለም አቀፍ ስታድየም የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን እንዲያዘጋጅ ተጠየቀ

ለሀገራችን የእግር ኳስ ዕድገት ዋነኛ እንቅፋቶች ውስጥ አንዱ የሆነው ደረጃውን የጠበቀ ሜዳ አለመኖር ሲሆን ይህንንም ችግር ለመቅረፍ እና ስደተኛው ብሔራዊ ቡድናችንን በሀገሩ ውድድር እንዲያደርግ በFIFA የወጣውን መስፈርት አሟልቶ ግንባታውን እያደረገ የሚገኘው የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታዎቹ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ ሲሆን የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ2ኛ ዙር ጀምሮ ውድድሮችን ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቆ መጨረሱ ተገልጿል።

የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ የሆኑት አቶ ጎሹ እንዳላማው ለክልሉ መገናኛ ብዙኀን እንደገለፁት “አሁን ላይ ባለው ሁኔታ ሀገራችን ላይ ካሉ የውድድር ሜዳዎች ምቹ እና ተመራጭ የሆነ ሜዳ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች በከተማችን ይገኛሉ። ውድድሩ እዚህ መካሄዱ የተዳከመውን የባህር ዳር ዳር ኢኮኖሚ ዳግም እንዲያንሰራራ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው። ውድድሩ ወደ ባህር ዳር እንዲመለስ ጥያቄዎችን አቅርበን መልስ እየጠበቅን ነው።” ሲሉ ሀሳቸውን ሰጥተዋል።

የውድድሩ የበላይ አካል በቀጣይ የሚሰጠውን ምላሽ አካተን የምንመለስ ይሆናል።

© Soccer Ethiopia

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahirdar City Foot Ball Referees & Commissioners Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Bahirdar City Foot Ball Referees & Commissioners Association:

Share

Category