AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት

AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት Ameco Sport Provides Real-time Sport updates.
(1)

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ባለድሉ ፒኤስ ጂ በገንዘብ ሽልማቱም ቀዳሚ ኾኗል።ባሕር ዳር፡ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ፍጻሜውን ባገኘው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ላይ የተሳተፉ ታ...
31/05/2026

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ባለድሉ ፒኤስ ጂ በገንዘብ ሽልማቱም ቀዳሚ ኾኗል።

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ፍጻሜውን ባገኘው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ላይ የተሳተፉ ታላላቅ ክለቦች እንደየደረጃቸው እና ካስመዘገቡት ውጤት ተነስተው የሚያገኙት የገንዘብ መጠን ይፋ ኾኗል።

የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር (ዩ ኢ ኤፍ ኤ) ለክለቦች የሚሰጠውን የሽልማት ገንዘብ የሚወሰነው በሦሥት ዋና ዋና መስፈርቶች ሲኾን እነሱም በውድድሩ ላይ እስከ የትኛው ደረጃ ድረስ እንደተጓዙ ክለቦቹ ባላቸው የ10 ዓመት የአውሮፓ ውድድሮች ደረጃ እና ከቴሌቪዥን ሥርጭት መብት ሽያጭ በሚገኝ ገቢ ላይ ተመስርቶ ነው።

ክለቦቹ ከውድድሩ ያገኙት የገንዘብ መጠን በደረጃ ሲቀመጥም

ፒኤስጂ 127 ሚሊዮን ፓውንድ፤ አርሰናል 124 ነጥብ 73 ሚሊዮን ፓውንድ፤ ባየር ሙኒክ 110 ነጥብ 84 ሚሊዮን ፓውንድ፤ ሊቨርፑል 95 ነጥብ 35 ሚሊዮን ፓውንድ፤ አትሌቲኮ ማድሪድ 90 ነጥብ 76 ሚሊዮን ፓውንድ፤ ሪያል ማድሪድ 90 ነጥብ 17 ሚሊዮን ፓውንድ፤ ባርሴሎና 86 ነጥብ 58 ሚሊዮን ፓውንድ፤ ማንቸስተር ሲቲ 84 ነጥብ 49 ሚሊዮን ፓውንድ፤ ቼልሲ 80 ነጥብ 210 ሚሊዮን ፓውንድ እና ቶተንሀም ሆትስፐር 74 ነጥብ 3 ሚሊዮን ፓውንድ ኾነው ተደልድለዋል።

እንደ ስካይ ስፖርት ዘገባ ይህ እጅግ ከፍተኛ የኾነ የገንዘብ ክፍያ ክለቦች በቀጣዩ የክረምት የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ ኾነው እንዲቀርቡ እና የፋይናንስ አቅማቸውን እንዲያጠናክሩ ትልቅ እገዛ ያደርግላቸዋል ሲል አስነብቧል።

በምስጋናው ብርሃኔ

#ስፖርት

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰአሚኮ_ዜናብ ይሁኑ !

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አሸነፈ። ፒኤስጂን ከአርሰናል ያገናኘው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በሀንጋሪ ቡዳፔስት ተካሂዷል። ፒኤስጂ ለተከታታይ ሁለት ዓመታት ነው ያ...
30/05/2026

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አሸነፈ።

ፒኤስጂን ከአርሰናል ያገናኘው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በሀንጋሪ ቡዳፔስት ተካሂዷል።

ፒኤስጂ ለተከታታይ ሁለት ዓመታት ነው ያሸነፈው። ከ20 ዓመታት በኋላ ለፍጻሜ የደረሰው አርሰናል ሳይሳካለት ቀርቷል።

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል። ፒኤስጂን ከአርሰናል ያገናኘው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በሀንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ ነው። ጨዋታው በ...
30/05/2026

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።

ፒኤስጂን ከአርሰናል ያገናኘው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በሀንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ ነው።

ጨዋታው በመደበኛው 90 ደቂቃ 1ለ1 ተጠናቅቋል። አርሰናል በመጀመሪያው አጋማሽ በካይ ሀቨርትዝ ግብ አማካኝነት 1ለ0 መርቶ ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ ፒኤስጂ በኦስሜን ዴንበሌ ግብ አቻ ኾኗል።

መደበኛ ዘጠና ደቂቃውም 1ለ1 ተጠናቅቋል። አሸናፊውን ክለብ ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል። በጭማሪው ደቂቃ ግብ ካልተቆጠረ ወደ መለያ ምት ያመራሉ።

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ አርሰናል ፒኤስጂን 1ለ0 እየመራ ነው። የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በሀንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ ነው። ጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቅ...
30/05/2026

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ አርሰናል ፒኤስጂን 1ለ0 እየመራ ነው።

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በሀንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ ነው።

ጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቅቋል። አርሰናል በካይ ሀቨርትዝ ግብ 1ለ0 እየመራ ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል። ጨዋታው በዚህ የሚጠናቀቅ ከኾነ አርሰናል በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን በማሸነፍ አዲስ ታሪክ ይጽፋል።

በጨዋታው ፔኤስጂ የኳስ ቁጥጥር የበላይነት አሳይቷል። ነገር ግን የአርሰናልን የመከላካል መስመር መስበር አልቻለም።

🇪🇹⚽️ ኢትዮጵያ ቡሩንዲን በደርሶ መልስ አሸነፈች።ባሕር ዳር፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመልስ ጨዋታ ኢትዮ...
30/05/2026

🇪🇹⚽️ ኢትዮጵያ ቡሩንዲን በደርሶ መልስ አሸነፈች።

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ ዛሬ ከቡሩንዲ ጋር በቡጁንቡራ ኢንትዋሪ ስታዲየም ላይ አድርጋ 2ለ1 አሸንፋለች።

የኢትዮጵያን የማሸነፊያ ግቦች በ53ኛው ደቂቃ ምኅረት አየለ እና በ73ኛው ደቂቃ ሊዲያ ኢያሱ አስቆጥረዋል።

በመጀመርያው ጨዋታ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ላይ ኢትዮጵያ 2ለ1 ማሸነፏ የሚታወስ ነው።

በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ በድምር ውጤት 4ለ2 በማሸነፍ ቀጣዩን የማጣርያ ዙር ተቀላቅላለች።

#ስፖርት #ኢትዮጵያ🇪🇹

በሮዛ የሻነህ

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰአሚኮ_ዜናብ ይሁኑ !

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

ሊቨርፑል አሠልጣኝ አርኔ ስሎትን አሰናበተ። ባሕር ዳር፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ)ሊቨርፑል አሠልጣኝ አርኔ ስሎትን አሰናብቷል። ከየርገን ክሎፕ ወርቃማ ዓመታት በኋላ ሊቨርፑልን የተ...
30/05/2026

ሊቨርፑል አሠልጣኝ አርኔ ስሎትን አሰናበተ።

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ)ሊቨርፑል አሠልጣኝ አርኔ ስሎትን አሰናብቷል።

ከየርገን ክሎፕ ወርቃማ ዓመታት በኋላ ሊቨርፑልን የተረከቡት አሠልጣኝ አርኔ ስሎት በመጡበት ዓመት የእንግሊዝ ፕሪምዬር ሊግ ዋንጫን አሸንፈዋል። በሁለተኛው የውድድር ዘመናቸው ግን ሊቨርፑል ተዳክሞ ታይቷል።

በርካታ ተጨዋቾችችን ያሰፈረመው ሊቨርፑል የበለጠ ተጠናክሮ ይቀርባል ሲባል ደካማ የውድድር ዓመትን አሳልፏል። ለሊቨርፑል መድከም ደግሞ ቀዳሚው ተጠያቁ አሠልጣኙ መኾናቸው ሲገለጽ ቆይቷል።

ሊቨርፑልም የክለቡን ጥንካሬ ዳግም ለመመለስ አሠልጣኙን ማሰናበቱን ዘ ሰን ስፖርት ዘግቧል። አሠልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ ሊቨርፑልን የሚረከቡት ቀዳሚው ምርጫ መኾናቸውን ፋብሪዚዮ ሮማኖ ጽፏል።

ክለቡ ሊቨርፑልም በድረ ገጹ በጋራው መረጃ አርኔ ስሎት ከዋና አሠልጣኝነት ሚናቸው መልቀቃቸውን አስታውቋል። እሳቸውን የሚተካ አሠልጣኝ የመቅጠር ሂደት መጀመሩን ገልጿል።

​አንድ የፕሪምዬር ሊግ ዋንጫ ላሸነፉት አሠልጣኙ ምስጋና እና አድናቆት እንዳለውም አስታውቋል።

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ !

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

30/05/2026

የዓለም ዋንጫ የምድብ አምስት ዳሰሳ

🏆 ⚽️ የክብሩን ዘውድ ማን ይጭነዋል ? ባሕር ዳር: ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) አርሰናል በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ፣ ፒኤስጂ ደግሞ በታሪኩ ለሁለተኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋን...
30/05/2026

🏆 ⚽️ የክብሩን ዘውድ ማን ይጭነዋል ?

ባሕር ዳር: ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) አርሰናል በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ፣ ፒኤስጂ ደግሞ በታሪኩ ለሁለተኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ለማሸነፍ ይፋለማሉ። አሁን ሚሊዮኖች ወደ ሀንጋሪዋ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ዓይናቸውን አዙረዋል። የአውሮፓ አሸናፊውን ክለብ የሚለየውን ጨዋታ ለመመልከት።

ፔኤስጂ በተከታታይ ዓመታት ዋንጫውን ከፍ ለማድረግ ቡዳፔስት ደርሷል። የእንግሊዝ ፕሪምዬር ሊግን ከ22 ዓመታት በኋላ ያሸነፈው አርሰናል ደግሞ ለሌላ ትልቅ ዋንጫ ወደ ቡዳፔስት አቅንቷል። አርሰናል በታሪኩ ለሁለተኛ ጊዜ ነው ለአውሮፓ ሻምፒዮናው ሊግ ፍጻሜ የደረሰው። ለመጀመሪያ ጊዜ ለፍጻሜ ደርሶ የነበረው እ.አ.አ በ2006 ነበር። አሁን ከ20 ዓመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ለፍጻሜ ደርሷል።

አርሰናል የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከኾነ የአውሮፓ ውድድሮችን ሁሉ የእንግሊዝ ክለቦች ያሸነፉበት ታሪክ ይጽፋሉ። የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን አስቶንቪላ፣ የዩሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ዋንጫን ክርስቲያል ፓላሰ አሸንፈዋል። አርሰናል ዛሬ ዋንጫውን የሚያሸንፍ ከኾነ የአውሮፓ ታላላቅ ዋንጫዎች ሁሉም ወደ እንግሊዝ ያቀናሉ።

ዛሬ በአውሮፓ ሻምፒዮናስ ሊግ ፍጻሜ የሚፋለሙት ሁለቱ ክለቦች ባለፈው ዓመት በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ላይ ተገናኝተው ነበር። ፒኤስጂ በሜዳው እና ከሜዳው ውጭ አርሰናልን በማሸነፍ ወደ ፍጻሜ መድረሱን ቢቢሲ አስታውሷል። በፍጻሜው ጨዋታም ድል በማድረግ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አሸንፏል።

አርሰናል በዛሬው ጨዋታ ድል የሚቀናው ከኾነ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ያሸነፈ 25ኛው ክለብ ይኾናል። በእንግሊዝ ደግሞ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግን ያሸነፈ ሰባተኛው ክለብ እንደሚኾን ቢቢሲ ዘግቧል።

እስካሁን ስድስት የእንግሊዝ ክለቦች የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን በማሸነፍ ቀዳሚዎች ናቸው። ከእንግሊዝ ውጭ ሌላ ሀገር ከሦስት የተለያዩ ክለቦች በላይ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ያሳካ የለም።

ያለ ምንም ዋንጫ በርካታ የአህጉራዊ ውድድሮችን ያደረገው አርሰናል ይሄን መጥፎ ታሪኩን ዛሬ ይሽረው ይኾን ? የሚለው ይጠበቃል።

አርሰናል በዘንድሮው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ያልተሸነፈ ብቸኛው ክለብ ነው። ዋንጫውን ለማሸነፍም ትክክለኛው ጊዜ ላይ ያለ ይመስላል።

ኢኤስፒኤን በዘገባው በአውሮፓ እግር ኳስ ምርጥ የማጥቃት እግር ኳስ የሚጫወተው ፒኤስጂ እና ምርጥ የመከላከል ጨዋታ የሚጫወተው አርሰናል በፍጻሜው ይገናኛሉ ይላል። ሁለት የተለያየ የአጨዋወት ስልት ያላቸው ክለቦች የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።

የሁለቱን ክለቦች ብቃት ሲገልጽ የማይገታው ኃይል ከማይንቀሳቀሰው አካል ጋር የሚጋጭበት ተደርጎ ይወሰዳል ይላል።

ቢሶከር በዘገባው ፒኤስጂ የሻምፒዮንስ ሊግ ዘውዳቸውን ለማስጠበቅ ዛሬ ትልቁን ፈተና ይጋፈጣሉ ብሏል። ታሪካዊ የኾነውን ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ድል ለመቀዳጀት አርሰናልን ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል። አርሰናልም የከብሩን ዘውድ ለመድፋት ይፋለማል።

የፒኤስጂውን አሠልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ በሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ላይ ከመወዳደር የበለጠ ትልቅ የማነቃቂያ ምንጭ የለም። ሌላው ነገር ሁሉ ከዚህ ጋር ሲነጻጸር ምንም ማለት ነው። ምርጥ ብቃት ማሳየት አለብን ብለዋል።

አርሰናሎች የዘንድሮውን የፕሪምዬር ሊግ ዋንጫ ድላቸው ለእኔ ምንም አያስደንቅም፤ ሙሉ በሙሉ የሚገባቸው አሸናፊዎች ናቸው፤ አስደናቂ የኾነ ወጥ አቋም አሳይተዋል፤ አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ በዚህ ክለብ ውስጥ የገነቡት ማንነት አሁን በግልጽ የሚታይ ኾኗል ብለዋል።

ባለፈው ዓመት ታሪክ ሠርተናል፤ ነገር ግን ዓላማችን ጽኑ ነው፤ እርሱም ራሳችንን ለረጅም ጊዜ በዓለም አቀፍ ታላላቅ ክለቦች ተርታ ማሰለፍ ነው፤ በድጋሚ ለፍጻሜ ደርሰናል፤ ይህ ለሁሉም ሰው ትልቅ ስኬት ነው፤ ለክለቡም ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ብለዋል።

ለፍጻሜ ጨዋታ የተለየ ዝግጅት እንደሚያስፈልግ የተናገሩት አሠልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ እንደዚህ አይነት አጋጣሚዎችን በአግባቡ መጠቀም ይገባል፤ እንዲህ አይነቱ ዕድል መቼ በድጋሜ እንደሚገኝ አይታወቅምና ነው ያሉት።

የአርሰናሉ አምበል ማርቲን ኦዲጋርድ ደግሞ ከ22 ዓመታት የዋንጫ ድርቅ በኋላ የፕሪምዬር ሊጉን ዋንጫ በድጋሚ አስመልሰናል፤ አሳክተነዋልም። ታሪክ መሥራታችንን መቀጠል እንፈልጋለን። ዋንጫ ማንሳት አስደናቂ ስሜት አለው፣ ይህም ለተጨማሪ ስኬት የበለጠ እንዲርበን ያደርገናል ብሏል።

በአርሰናል ታሪክ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግን ወደ ኤምሬትስ ስታዲየም ለማምጣት ያለውን ተስፋም ገልጿል።

የአርሰናሉ አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው በጥሩ ዝግጅት ላይ እንደኾነ ገልጸዋል። ዋንጫውን ወደ ለንደን ለማምጣት እንደሚጫወቱም ተናግረዋል። የዛሬው ጨዋታ በእግር ኳስ ትልቁ ጨዋታ እንደኾነ እናውቃለን፤ የዚህ ክብር ታሪክ ባለቤት መኾን እንፈልጋለን ነው ያሉት።

በታሪካችን ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ እዚህ ስንመጣ በክለቡ ታሪክ ውስጥ አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ነው። አዲስ ታሪክ ለመጻፍ እንደተቃረብን እናምናለን ብለዋል።

ዛሬ የክብሩን ዘውድ ማን ይጭናል ? አርሰናል ወይስ ፒኤስጂ በጉጉት ይጠበቃል። ይህ አጓጊ የፍጻሜ ጨዋታ በሀንጋሪ ፑሽካሽ አሬና ምሽት 1:00 ላይ ይካሄዳል።

በታርቆ ክንዴ

#አሚኮ-ዜና #ስፖርት #

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

30/05/2026

የዓለም ዋንጫ የምድብ ሦስት ዳሰሳ

🇪🇹⚽️ ኢትዮጵያ ዛሬ ቡሩንዲን ትገጥማለች።ባሕር ዳር፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ ዛሬ...
30/05/2026

🇪🇹⚽️ ኢትዮጵያ ዛሬ ቡሩንዲን ትገጥማለች።

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የሁለተኛ ዙር ማጣርያ የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ ዛሬ ቡጁንቡራ ኢንትዋሪ ስታዲየም ላይ ቡሩንዲን ቀን 10:00 ላይ ትገጥማለች።

በመጀመርያው ጨዋታ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ላይ ኢትዮጵያ 2ለ1 ማሸነፏ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በድረ ገጹ እንዳስነበበው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ በጨዋታው ሙሉ ቢጫ መለያ ለብሶ ወደ ሜዳ ይገባል።

#ስፖርት #ኢትዮጵያ🇪🇹

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ !

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !*

Address

Bahirdar
Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት:

Share

Category