AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት

AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት Ameco Sport Provides Real-time Sport updates.
(1)

አርሰናል ቡሩኖ ጉማሬሽን ለማስፈረም ሙሉ ስምምነት ላይ ደረሰ።መድፈኞቹ የኒውካስትሉ ብራዚላዊ የመሐል ሜዳ ተሰላፊ ቡሩኖ ጉማሬሽን ለማስፈረም ሙሉ በሙሉ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ለንደን ኢ...
01/08/2026

አርሰናል ቡሩኖ ጉማሬሽን ለማስፈረም ሙሉ ስምምነት ላይ ደረሰ።

መድፈኞቹ የኒውካስትሉ ብራዚላዊ የመሐል ሜዳ ተሰላፊ ቡሩኖ ጉማሬሽን ለማስፈረም ሙሉ በሙሉ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ለንደን ኢቭኒንግ ዘግቧል።

እንደ ሜትሮ እና ሚረር ያሉ የመረጃ ምንጮች እንደዘገቡት አርሰናል 70 ሚሊዮን ፓውንድ ለኒውካስትል አስቀድሞ የሚከፍል ሲኾን ከተጫዋቹ እና ከክለቡ ስኬት ጋር የተያያዘ 10 ሚሊዮን ፓውንድ ተጨማሪ ክፍያም በስምምነቱ ውስጥ ተካትቷል።

የፈረንሳዩ ሌኪፕ ጋዜጣ በበኩሉ አርሰናል ጉማሬሽን በ90 ሚሊዮን ዩሮ ለማስፈረም እንደተስማማ መረጃ አውጥቷል።

በግል ጥቅማጥቅ ዙሪያ ቀደም ብሎ ከስምምነት ላይ የደረሰው ተጫዋቹ የመድፈኞች ሦሥተኛው የክረምት ፈራሚ ለመኾን በዚህ ሳምንት ወደ ለንደን ተጉዞ የሕክምና ምርመራውን እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

ከቀናት በፊት የኒውካስትል ዩናይትዱ ዋና አሠልጣኝ ከክለቡ ጋር በስምምነት ለመለያዬት የወሰኑት እንደ አንቶኒ ጎርደን እና ሳንድሮ ቶናሊ ያሉ ቁልፍ ተጫዋቾች ክለቡን መልቀቃቸው ሳያንስ የጉማሬሽን መልቀቅ አይቀሬ መኾኑን በመረዳታቸው እንደኾነ ሲነገር ቆይቷል።

ተጫዋቹ ለቅድመ ውድድር ዝግጅት ወደ ስፔን በረራ ካደረገው የኒውካስትል ቡድን ሥብሥብ ውስጥ እንዳልተገኘ እና ዝውውሩን በማጠናቀቅ ላይ መኾኑን ዘጋርዲያን ዘግቧል።





በአድኖ ማርቆስ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ላይ ዕምነት እንደሌለው ገለጸ።የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ የዓለም ዋንጫን የንግድ ድርሻ ወይም "ፊፋ ፎርዋርድ ...
01/08/2026

የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ላይ ዕምነት እንደሌለው ገለጸ።

የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ የዓለም ዋንጫን የንግድ ድርሻ ወይም "ፊፋ ፎርዋርድ ኢንተርፕራይዝ" በሚል አዲስ ዕቅድ ለግል ባለሀብቶች ለመሸጥ አቅደው እንደነበር ይታወሳል።

የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን፣ የሰሜን፣ የመካከለኛው አሜሪካ እና የካሪቢያን እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ዕቅዱን "በስውር የተጠነሰሰ እና ግልጽነት የጎደለው ስምምነት" ነው በማለት በዕቅዱ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ አሰምተዋል።

የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ዕቅዱ ካልተሰረዘም የዓለም ዋንጫን ጨምሮ በማንኛውም የፊፋ ውድድሮች ላይ ላለመሳተፍ በአንድ ድምጽ ወስኖ እንደነበርም ቢቢሲ ዘግቧል።

ፊፋ ከቀረበበት ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ተቃውሞ እና ከውስጥ የባለሥልጣናት መልቀቅ በኋላ የዓለም ዋንጫን ድርሻ የመሸጥ ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ለመሰረዝ ተገድዷል።

የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ባወጣው መግለጫ ዕቅዱ ቢሰረዝም “የአሁኑ የፊፋ አመራር የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበርን ብቻ ሳይኾን የሌሎችን የእግር ኳስ ቤተሰቦች ዕምነት አጥቷል” በማለት ለጂያን ኢንፋንቲኖ የሚሰጠውን ድጋፍ ማንሳቱን አረጋግጧል።

እንደ ብሪታኒያው ዘ ቴሌግራፍ እና ጎል ዶት ኮም ዘገባ ደግሞ የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ኀላፊነታቸውን እንዲለቁ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

ኢንፋንቲኖ በገዛ ፈቃዳቸው ኀላፊነታቸውን የማይለቁ ከኾነም የማኅበሩ 55 አባል ሀገራት እሱን ከሥልጣን ለማስወገድ የሚያስችል ድምጽ ለመስጠት ዝግጁ መኾናቸውን ገልጸዋል።

ድምጽ መስጠቱን በይፋ ለመጀመር ከፊፋ 211 አባላት መካከል የ43 ሀገራት ድጋፍ ብቻ የሚያስፈልግ ሲኾን የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ይህንን በቀላሉ ማሠባሠብ እንደሚችል ገልጿል።





በአድኖ ማርቆስ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

01/08/2026

የብሩኖ ጉማሬሽ እና ሌሎች የዝውውር መረጃዎች

በታማኝነት የተጠናቀቀ ሕይወት እና የወንድማማቾቹ ልብ ሰባሪ መለያየት።በጣሊያን እግር ኳስ ዛሬ ከባድ ቀን ኾኗል። የኤሲ ሚላን ምልክት የኾነው ፍራንኮ ባሬዚ በ66 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተ...
31/07/2026

በታማኝነት የተጠናቀቀ ሕይወት እና የወንድማማቾቹ ልብ ሰባሪ መለያየት።

በጣሊያን እግር ኳስ ዛሬ ከባድ ቀን ኾኗል። የኤሲ ሚላን ምልክት የኾነው ፍራንኮ ባሬዚ በ66 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ፍራንኮ በታማኝነቱ፣ ከገዛ ወንድሙ ጋር በነበረው ታሪካዊ ፍጥጫ እና ባስመዘገባቸው ድንቅ ስኬቶች ሁልጊዜም በእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በክብር የሚታወስ ጀግና ነው።

ፍራንኮ እና ወንድሙ ጁሴፔ ለሁለት ተቀናቃኝ ክለቦች ያደረጉት ፍልሚያ በእግር ኳስ ዓለም ውስጥ ፈጽሞ የሚደገም አይመስልም።

ፍራንኮ የ20 ዓመታት የእግር ኳስ ሕይወቱን ለኤሲ ሚላን ሲያገለግል፣ ታላቅ ወንድሙ ጁሴፔ ባሬዚ ደግሞ ለባላንጣው ኢንተር ሚላን ለ16 ዓመታት ተጫውቷል።

በታማኝነት የታነፀው ፍራንኮ የሌላ ክለብ ማልያ ሳይለብስ ነው ጫማ የሰቀለው።

በተለይ ሁለቱ ወንድማማቾች በወቅቱ ከባድ በነበረው የ"ደርቢ ዲ ማዶኒና" (የሚላን ደርቢ) ጨዋታ ላይ የየቡድኖቻቸው አምበል ኾነው መሐል ሜዳ ላይ ሲገናኙ፣ ፈገግ ብለው የክለብ አርማ ሲለዋወጡ ማየት ለተመልካቾች አስገራሚ ነበር።

የፍራንኮ ባሬዚ ስኬት እና የ6 ቁጥር መለያ ዘላለማዊ እግድ

ፍራንኮ በኤሲ ሚላን በቆየባቸው 20 ዓመታት ውስጥ 17 ትልልቅ ዋንጫዎችን አጣጥሟል። በተለይም ክለቡ በውጤት ማጣት እና በቅሌት ምክንያት ሁለት ጊዜ ወደ ሁለተኛው ዲቪዚዮን በወረደበት አስቸጋሪ ወቅት በክለቡ በመቆየት ተወዳዳሪ የሌለው ታማኝነቱን አስመስክሯል።

ኤሲ ሚላንን ለ15 ዓመታት በአምበልነት የመራው ፍራንኮ 6 የሴሪ ኤ እና 3 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን ማሸነፍ ችሏል።

ለዚህ ታማኝነቱ እና ለከፈለው መስዋዕትነት ክብር ሲልም ኤሲ ሚላን እርሱ የለበሰውን ታሪካዊውን የ6 ቁጥር መለያ ማንም እዳይለብሰው ለዘላለም አግዶታል።

በብሔራዊ ቡድን ደረጃም ለጣሊያን 81 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲኾን የ1982ቱን የዓለም ዋንጫ ድል አሳክቷል። በተጨማሪም በዓለም ዋንጫ ታሪክ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ በማግኘት ብቸኛው ስሙን በወርቅ የፃፈ ጣሊያናዊ ተጫዋች ነው።

በወንድሙ ጥላ ያልተከለለው ጁሴፔ እና ልብ ሰባሪው ስንብት

በታናሽ ወንድሙ ጥላ ያልተሸፈነው ጁሴፔ ባሬዚም በኢንተር ሚላን በዋንጫ የታጀበ ታላቅ ስኬት አስመዝግቧል። ኾኖም ዛሬ በሜዳ ላይ ጠንካራ ባላንጣው፣ በቤት ውስጥ ግን አብሮ አደግ ወንድሙ የኾነው ፍራንኮ በሕይወት ተለይቶታል።

"እርሱ ወንድሜ ብቻ ሳይኾን፣ ጀግናዬ እና በህይወቴ ካየኋቸው ምርጥ ተፋላሚዎቼ አንዱ ነበር" በማለት ሀዘኑን ገልጿል።

በስኬት የደመቀው እና በታማኝነት የፀናው የባሬዚ ወንድማማቾች የእግር ኳስ ታሪክ ዛሬ ጥቁር ቀን ገጥሞታል።

#አሚኮ #ስፖርት



✍️ በንዋይ ሙሉጌታ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

31/07/2026

የኒውካስትል ዩናይትድ የምጥ መጀመሪያ

የአርሰናል ባለሀብቶች በቪኒሽየስ ዝውውር ጉዳይ በድንገት እጃቸውን አስገቡ።ሪያል ማድሪድ የብራዚላዊውን ኮከብ ውል ለማራዘም ቢጥርም በደሞዝ ጉዳይ እስካሁን ድረስ አልተስማሙም።ቪኒሽየስ ውሉን ...
31/07/2026

የአርሰናል ባለሀብቶች በቪኒሽየስ ዝውውር ጉዳይ በድንገት እጃቸውን አስገቡ።

ሪያል ማድሪድ የብራዚላዊውን ኮከብ ውል ለማራዘም ቢጥርም በደሞዝ ጉዳይ እስካሁን ድረስ አልተስማሙም።

ቪኒሽየስ ውሉን የማያድስ ከኾነ ከአንድ ዓመት በኋላ ማድሪድ ድምቡሎ ሳያገኝ ተጫዋቹን ያጣዋል።

ይህንን ክፍተት ተጠቅመው አርሰናሎች ተጫዋቹን ወደ ለንደን ለማስኮብለል እየሠሩ ነው።

ያሆ ስፖርት እንደዘገበው የአርሰናል ባለቤቶች የክሮንኬ ቤተሰቦች ከቪኒሽየስ ወኪል"ሮክ ኔሽንስ" ጋር ተወያይተዋል።

ባለሀብቶቹ ክለቡን በሱ ዙሪያ ለመገንባት ስለያዙት ኘሮጀክት እና በሳምንት እስከ 400ሺህ ፖውንድ ደሞዝ ለመክፈል መዘጋጀታቸውን ለወኪሉ አብራርተዋል።

ያም ኾኖ የቪኒሽየስ ጁኒየር ተቀዳሚ ምርጫው የማድሪዱ ክለብ መኾኑን ዘገባው አመላክቷል።

#አሚኮ #ስፖርት



በንዋይ ሙሉጌታ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

የአርጀንቲናን የእግር ኳስ ዘረኝነት ይገታል ተብሎ የሚገመተው ታምረኛው ኪኪ ራሞስከሰሞኑ በወዳጅነት ጨዋታ የአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ኢኳዶርን 2 ለ 1 አሸንፏል።    በጨ...
30/07/2026

የአርጀንቲናን የእግር ኳስ ዘረኝነት ይገታል ተብሎ የሚገመተው ታምረኛው ኪኪ ራሞስ

ከሰሞኑ በወዳጅነት ጨዋታ የአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ኢኳዶርን 2 ለ 1 አሸንፏል።

በጨዋታው አንድ ኪኪ ራሞስ የተባለ ጥቁር ተጫዋች አርጀንቲናን ወክሎ ተጫውቷል።

ጥቁሮችን በሚያገለው የአርጀንቲና ቡድን ከ44 ዓመታት በኋላ ጥቁር ተጫዋች መታየቱ እንግዳ በመኾኑ መነጋገሪያ ኾኗል።

ነገሩ እንዲህ ነው_ በ2010 በሀይቲ ከ300 ሺህ በላይ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው የመሬት መንቀጥቀጥ አይዘነጋም፤ ከዚህ አስከፊ አደጋ አንድ የ8 ወር ሕጻን በተአምር በሕይወት ተገኝቷል።

ወላጆቹን በአደጋው የተነጠቀው ይህ ሕጻን በማደጎ የማደግ ዓለም የሰጠችው እጣ ፋንታ ኾኗል።

የእግር ኳስ ተሰጥኦን ይዞ የተወለደው ይህ ሕጻን ዕድል እና አጋጣሚ ሰምሮለት አሳዳጊዎቹ ከእግር ኳሷ ምድር የበቀሉ አርጀንቲናውያን ናቸው።

ይህ ጥቁር ሕጻን ዛሬ ላይ አድጎ እና በክህሎት ጎልብቶ ነው እንግዲህ የአርጀንቲናን መለያ ለመልበስ የበቃው።

ጥቁሮችን በአርጀንቲና መለያ ያልለመደው እግር ኳስ አፍቃሪ እና ሚዲያ ጉዳዩን መነጋገሪያ አድርጎታል።

ታዳጊው ኪኪ ራሞስ በክህሎቱ አሳምኖ በአንድ ክፍለ ዘመን "ላ አልቢሰለስቴዎች"ን የወከለ 4ኛው ጥቁር ተጫዋች ኾኗል።

ከ1978 የዓለም ዋንጫ በኋላ ለጥቁሮች ባይተዋር የኾነው የአርጀንቲና እግር ኳስም ነገሩ ከዘረኝነት ትችት ማምለጫ መንገድ ኾኖለታል።

​​ #አሚኮ #ስፖርት



በንዋይ ሙሉጌታ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

30/07/2026

ለመገመት አዳጋቹ መጭው ፕሪሚየር ሊግ

በብዙ ክለቦች ሲፈለግ የነበረው ማክሰንስ ላኮሪስ ቸልሲን ተቀላቀለ።በቅርቡ ዣቪ አሎንሶን ዋና አሠልጣኝ አድርጎ የሾመው የምዕራብ ለንደኑ የእግር ኳስ ቡድን ቸልሲ በክረምቱ የዝውውር መስኮት በ...
30/07/2026

በብዙ ክለቦች ሲፈለግ የነበረው ማክሰንስ ላኮሪስ ቸልሲን ተቀላቀለ።

በቅርቡ ዣቪ አሎንሶን ዋና አሠልጣኝ አድርጎ የሾመው የምዕራብ ለንደኑ የእግር ኳስ ቡድን ቸልሲ በክረምቱ የዝውውር መስኮት በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል።

ሞርጋን ሮጀርስን እና ዳኒ ዌልቤክን ያስፈረመው እኔዲኹም ከጆርዳን ሄንደርሰንን ጋር የቃል ስምምነት ላይ የደረሰው ቸልሲ አሁን ደግሞ የ26 ዓመቱን የክርስቲያል ፓላስ ተከላካይ ማክሰንስ ላኮሪስን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

ቸልሲ ለዝውውሩ 52 ሚሊየን ፓውንድ ለክርስቲያል ፓላስ ይከፍላል። ተጫዋቹ በስታፎርድ ብሪጅ ለስድስት ዓመታት የሚያቆየውን የረጅም ጊዜ ውል መፈራረሙ ነው የተገለጸው።

ማክሰንስ የቀድሞ ክለቡ ክርስቲያል ፓላስ የኤፍኤ እና ኮንፈረንስ ሊግ ዋንጫዎችን እንዲያሸንፍ ከፍተኛ ሚና በመጫወቱ በትላልቅ ክለቦች ዕይታ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል። በዣቪ አሎንሶ የጨዋታ ፍልስፍና የቸልሲን የመሃል ተከላከይ መስመር ክፍተት ለመሙላት ትልቅ አቅም ኾኖ እንደሚያገለግልም ይጠበቃል።

ተጫዋቹ እንደ ሊቨርፑል እና ባየርንሙኒክ ባሉ ታላላቅ የእግር ኳስ ቡድኖች በጥብቅ ሲፈለግ ነበር።



በአድኖ ማርቆስ

30/07/2026

አወዛጋቢው የፊፋ አዲሱ እቅድና የአባል ኮንፌዴሬሽኖች ምላሽ

Address

Bahirdar, Ethiopia
Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AMECO Sport - አሚኮ ስፖርት:

Shortcuts

Share

Category