07/03/2022
#መረጃ ለባህር ዳር ነዋሪዎች በሙሉ፦
የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በነገው ዕለት በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተመጣጣኝ ዋጋ የዘይት ስርጭት ያካሄዳል።
መንግስት በአገራችን የተከሰተው የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት የተለያዩ ሥራወችን በመስራት ላይ የሚገኝ ቢሆንም በህብረተሰቡ ላይ ያለው ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው።በተለይም ደግሞ በምግብ እህሎችና የምግብ ዘይት ላይ የዋጋ ጭማሪ ተከስቷል። መንግስት ይህንን ለማረጋጋት ከሚያደረገው እንቅስቃሴ በተጨማሪ ችግሩን ለመቀነስ በከተማ አስተዳደሩ ሁለት መሠረታዊ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ።
ይኸውም.....
1ኛ/ የባህር ዳር ከተማ አስተዳድር ከንቲባ ኮሚቴ በአደረገው አስችኳይ ስብሰባ እንደ ከተማ አስተዳደር ለሸማቾች ህብረት ስራ ዩኒየን 10 ሚሊዮን ብር ተዘዋዋሪ ብድር በጀት በመመድበ ፣የግብርና ምርቶችና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተለይም መሠረታዊ የፍጁታ ዕቃዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ ሥራ የተሠራ ሲሆን በተመጣጣኝ ዋጋ ምግብ የሚሸጡ ቢያንስ በሶስት ክፍለ ከተሞች የቀበሌ ምግብ ቤቶችንና ስጋ ቤቶችን እንዲከፍቱ ድጋፍ እየተደረገ ነው።
2ኛ/ በበላየነህ ክንዴ ለከተማችን የሚቀርበው የፊቤላ ዘይት በወቅቱና በበቂ መጠን እየቀረበ ባለመሆኑ ከክልሉ ንግድ ቢሮ ጋር በመነጋገር 883,000 ሊትር ፓልም ዘይት ከውጭ ተገዝቶ በአለ በጅምላ በኩል ቀርቧል። በመሆኑም በነገው ዕለት በሁሉም ክፍለ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የዘይት ስርጭት ያካሄዳል።
ስለሆነም መንግስት ከሚያደርገው የቁጥጥር ሥራ በተጨማሪ አቅርቦቱ ላይ ያለውን ችግር ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ስለሆነ የከተማችን ነዋሪዎች በተፈጠረው ያልተገባ የዋጋ ንረት ያላስፈላጊ ወጭ እንዳትዳረጉ ከተማ አስተዳደሩ በጥብቅ እያሳሰበ ለሚደረገው የህግ ማስከበር ሥራ አስፈላጊውን ትብብር እንድታደርጉ ጥሪውን ያስተላልፋል።
#የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር