Ethio Sport 343 ኢትዮ ስፖርት 343

Ethio Sport 343 ኢትዮ ስፖርት 343 "Join the Ethio Sport 343 family for the latest, breaking sports news along with in-depth analysis." ወቅታዊና ትኩስ ስፖርታዊ መረጃዎች ወደ እናንተ እናደርሳለንደርሳለን

አርባምንጭ ከተማ የሁለት ተጫዋቾችን ውል አደሰለተጨማሪ 2 ዓመት የሚያቆየውን ውል ለማደስ የተስማማው የክለቡ አንበልና የኋላ ደጀኑ አሸናፊ ፊዳ ነው ።ሌላኛው ደግሞ ከታዳጊ ቡድን ጀምሮ በዋና...
01/08/2026

አርባምንጭ ከተማ የሁለት ተጫዋቾችን ውል አደሰ

ለተጨማሪ 2 ዓመት የሚያቆየውን ውል ለማደስ የተስማማው የክለቡ አንበልና የኋላ ደጀኑ አሸናፊ ፊዳ ነው ።

ሌላኛው ደግሞ ከታዳጊ ቡድን ጀምሮ በዋናው ቡድን ያገለገለውን ግብ ጠባቂ ሰራዊት ሴያ ሲሆን በክለቡ ለተጨማሪ 2 ዓመት የሚያቆየውን ውል ለማደስ በዛሬው ዕለት ተስማምቷል ።

ብሩክ በየነ ወደ እናት ክለቡ ተመልሷል!ሀዋሳ ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ሦስተኛውን ፈራሚ የገኘ ሲሆን የቀድሞ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል።በዛሬው ዕለት ወደ ዝውውሩ ከገቡ በኋላ ከሀድያ ሆሳዕና ቃለ...
01/08/2026

ብሩክ በየነ ወደ እናት ክለቡ ተመልሷል!

ሀዋሳ ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ሦስተኛውን ፈራሚ የገኘ ሲሆን የቀድሞ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል።

በዛሬው ዕለት ወደ ዝውውሩ ከገቡ በኋላ ከሀድያ ሆሳዕና ቃለአብ ውብሸት እና ሙሴ ካቤላን ያስፈረሙት ሀዋሳ ከተማዎች የቀድሞው የወልቂጤ ከተማ ፣ ሀዋሳ ከተማ እና ያለፉትን ሁለት አመታት በሀድያ ሆሳዕና መጫወት የቻለውን የቀድሞው አጥቂያቸው ብሩክ በየነን በሁለት አመት ውል አስፈርመዋል።

🚨 አዲስ መረጃ፡ ሪል ማድሪድ ለቪኒሲየስ ጁኒየር የመጨረሻ የኮንትራት ማሻሻያ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ ጥያቄውን የማይቀበለው ከሆነ ግን ለመሸጥ ተዘጋጅቷል።የክለቡ ባለስልጣናት ለቪኒሲየስ ወኪሎች...
01/08/2026

🚨 አዲስ መረጃ፡ ሪል ማድሪድ ለቪኒሲየስ ጁኒየር የመጨረሻ የኮንትራት ማሻሻያ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ ጥያቄውን የማይቀበለው ከሆነ ግን ለመሸጥ ተዘጋጅቷል።

የክለቡ ባለስልጣናት ለቪኒሲየስ ወኪሎች ከዚህ የተሻለ ሌላ ጥያቄ እንደማይቀርብ አሳውቀዋል። ተጫዋቹ የቀረበለትን ውል መቀበል አለዚያም ኮንትራቱ ወደ መጨረሻው ዓመት ከመግባቱ በፊት የዝውውር አማራጭን መጋፈጥ ይኖርበታል።

ማድሪድ ብራዚላዊው ተጫዋች ውሉን ሳያድስ እስከ ጃንዋሪ 2027 እንዲቆይ አይፈልግም፤ ምክንያቱም በዚያን ጊዜ ከሌሎች ክለቦች ጋር በነፃ ዝውውር (Free Transfer) ለመደራደር እድል ያገኛል።

ክለቡ ጥብቅ ቋሚ አቋም ቢይዝም፣ የዝውውር መስኮቱ ከመዘጋቱ በፊት በቪኒሲየስ የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ይደረሳል በሚል ተስፋ በሁለቱ ወገኖች መካከል የሚደረገው ድርድር በሚቀጥሉት ቀናት እንደሚቀጥል ተጠብቋል።

ሽመልስ በቀለ የጣና ሞገዶቹ ለመቀላቀል ተቃርቧል !ባለፉት ሁለት ዓስርት ዓመታት ከታዩ ምርጥ አማካዮች አንዱ የሆነው ሽመልስ በቀለ ወደ የጣና ሞገዶቹ ለመቀላቀል ተቃርቧልከሀዋሳ ከተማ ጋር ለ...
01/08/2026

ሽመልስ በቀለ የጣና ሞገዶቹ ለመቀላቀል ተቃርቧል !

ባለፉት ሁለት ዓስርት ዓመታት ከታዩ ምርጥ አማካዮች አንዱ የሆነው ሽመልስ በቀለ ወደ የጣና ሞገዶቹ ለመቀላቀል ተቃርቧል

ከሀዋሳ ከተማ ጋር ለሁለት ዓመታት ለመቆየት የሚያስችል የውል ስምምነት ቢኖረውም በቅርቡ የመልቀቂያ ደብዳቤ አስገብቶ ከሐይቆቹ ጋር በስምምነት የተለያየው ሽመልስ በቀለ መዳረሻው ባህር ዳር ከተማ ለመሆን መቃረቡን ሶከር ኢትዮጵያ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ታማኝ ምንጮቿ አረጋግጣለች።

የእግርኳስ ህይወቱን በኮረም ሜዳ የጀመረው አማካዩ ሽመልስ በቀለ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨምሮ በክለብ ደረጃ በሀዋሳ ከተማ፣ በቅዱስ ጊዮርጊስ በማስከተል ከሀገር ውጭ ለሱዳኑ ኤል ሜሪክ እና ለሊብያው አል ኢትሀድ እንዲሁም ድፍን አስር ዓመታት ወደ ቆየበት ግብፅ በማቅናት የክለቡ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በሆነበት እና በአምበልነት ያገለገለበትን ፔትሮጀት ጨምሮ በኤል ጎውና ፣ ምስር አል መቃሳ እና ኤን ፒፒ አይ በመጫወት ከኢትዮጵያ ውጭ የእግርኳስ ህይወቱን ካጠናቀቀ በኋላ ወደ ሀገር ቤት በመመለስ ለመቻል እንዲሁም ወደ ቀድሞ ክለቡ ሀዋሳ ከተማ ለአንድ ዓመት ሲጫወት ቆይቶ አሁን ደግሞ ወደ ጣና ሞገዶቹ ለማቅናት መስማማቱ እርግጥ ሆኗል።

ዛሬ የሚደረጉ ተጠባቂ የወዳጅነት ጨዋታዎች  🚩ቼልሲ  6፡30 ቶተንሃም  🚩ማንቼስተር ሲቲ 8፡30 ኢንተር ሚላን  🚩ማንቼስተር ዩናይትድ 10፡00 አትሌትኮ ማድሪድ  🚩ጂሮና 3፡00 አርሰናልE...
01/08/2026

ዛሬ የሚደረጉ ተጠባቂ የወዳጅነት ጨዋታዎች

🚩ቼልሲ 6፡30 ቶተንሃም
🚩ማንቼስተር ሲቲ 8፡30 ኢንተር ሚላን
🚩ማንቼስተር ዩናይትድ 10፡00 አትሌትኮ ማድሪድ
🚩ጂሮና 3፡00 አርሰናል
Ethio Sport 343 ኢትዮ ስፖርት 343
Tribune SPORT with Fikir Yilikal and Ephrem Yemane
Mensur Abdulkeni
DAGU SPORT ዳጉ ስፓርት

ያል ማድሪድ ለቪኒሲየስ ጁኒየር ሲል የደመወዝ ጣሪያውን እንደማያፈርስ ገለጸ የስፓኞሉ ጋዜጣ «ማርካ» (Marca) እንደዘገበው፣ ሪያል ማድሪድ የብራዚሊያዊውን የክንፍ አጥቂ ቪኒሲየስ ጁኒየርን...
31/07/2026

ያል ማድሪድ ለቪኒሲየስ ጁኒየር ሲል የደመወዝ ጣሪያውን እንደማያፈርስ ገለጸ

የስፓኞሉ ጋዜጣ «ማርካ» (Marca) እንደዘገበው፣ ሪያል ማድሪድ የብራዚሊያዊውን የክንፍ አጥቂ ቪኒሲየስ ጁኒየርን አስፈላጊነት እና የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋችነት ቢረዳም፣ ለየትኛውም ተጫዋች ሲል የክለቡን የደመወዝ መዋቅር (Wage Structure) እንደማያፈርስ ግልጽ አድርጓል።

ትሁን አየለ ሸገር ከተማን ተቀላቀለች !የቀድሞ አርባምንጭ ከተማ (እንስት አዞዎቹ) ተጫዋች ሆና በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ እየተጫወተች የቆየችው ትሁን አየለ ማረፊያዋ ሸገር ከተማ ሆኗል...
31/07/2026

ትሁን አየለ ሸገር ከተማን ተቀላቀለች !

የቀድሞ አርባምንጭ ከተማ (እንስት አዞዎቹ) ተጫዋች ሆና በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ እየተጫወተች የቆየችው ትሁን አየለ ማረፊያዋ ሸገር ከተማ ሆኗል፡፡

ሚካይሎ ሙድሪክ ወደ ሜዳ እንዲመለስ ተፈቀደለት​የቼልሲው የፊት መስመር ተጫዋች ሚካይሎ ሙድሪክ በፀረ አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት ምክንያት የተጣለበት የ4 ዓመት እግድ መነሳቱን ተከትሎ ወደ...
31/07/2026

ሚካይሎ ሙድሪክ ወደ ሜዳ እንዲመለስ ተፈቀደለት

​የቼልሲው የፊት መስመር ተጫዋች ሚካይሎ ሙድሪክ በፀረ አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት ምክንያት የተጣለበት የ4 ዓመት እግድ መነሳቱን ተከትሎ ወደ እግር ኳስ እንዲመለስ ተፈቀደለት።

​የእንግሊዝ እግር ኳስ ማኅበር እና ዓለም አቀፉ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ ዩክሬናዊው ተጫዋች ላይ ተጥሎ የነበረውን የዶፒንግ ህግ ጥሰት እግድ ለማንሳት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

​ሙድሪክ እ.አ.አ. በ2024 በተደረገበት የተለመደ የሽንት ምርመራ የ"ሜልዶኒየም" ንጥረ ነገር በመገኘቱ ምክንያት በጊዜያዊነት ከእግር ኳስ ታግዶ እንደነበር ይታወሳል።

​ሆኖም የእንግሊዝ እግር ኳስ ማኅበር እንደገለፀው ከሆነ፣ በዓለም አቀፉ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ ቴክኒካል መመሪያዎች ላይ በተደረጉ ለውጦች ምክንያት ተጫዋቹ የሰጠው ናሙና አሁን ባለው ህግ መሰረት ምንም አይነት የዶፒንግ ህግ ጥሰት ውጤት አይኖረውም።

​ከ2024 ጀምሮ ለቼልሲ ያልተጫወተው የ25 ዓመቱ ተጫዋች፣ ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ከሜዳ ርቆ ከቆየ በኋላ አሁን ወደ ሜዳ እንዲመለስ ተፈቅዶለታል።

2016 ቻምፒዮኖቹ ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የአራት ነባር ተጫዋቾች ውል በማራዘም ወደ ዝውውሩ መግባት ችለዋል።በአሰልጣኝ በጸሎት ልዑልሰገድ የሚመሩት ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የአራት ነባር ተጫ...
31/07/2026

2016 ቻምፒዮኖቹ ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የአራት ነባር ተጫዋቾች ውል በማራዘም ወደ ዝውውሩ መግባት ችለዋል።

በአሰልጣኝ በጸሎት ልዑልሰገድ የሚመሩት ኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የአራት ነባር ተጫዋቾቻቸውን ውል በማራዘም ወደ ዝውውሩ መግባታቸው ታውቋል።

ከታዳጊ ቡድን ያደገው እና ዘንድሮ የመሰለፍ ዕድል ያገኘው ተስፈኛው ግብ ጠባቂ አማኑኤል ደስታ፣ ከተስፋ ቡድኑ ያደገው እና በዚህ በተጠናቀቀው ዓመት ለመጀመርያ ጊዜ መጫወት የቻለው ተስፈኛው የቀኝ መስመር ተከላካይ አቤኔዜር ተክሉ፣ ንግድ ባንክ ወደ ሊጉ ሲያድግ ቁልፍ ሚና የነበረው እና ያለፉትን ሁለት ዓመታት ከቡድኑ ጋር የቆየው ዘንድሮ ባመዛኙ ጨዋታዎች ላይ መሳተፍ የቻለው አማካዩ ብሩክ ብፁዕአምላክ እና ባለ ተሰዕጦው ዓምና ከተስፋ ቡድን በማደግ ተስፋ ሰጪ ዕድገት እያሳየ የሚገኘው አማካይ ዮሐንስ ኪዳኔ በቡደኑ ለተጨማሪ ዓመት ለመቆየት ውል ማራዘሙ ተጫዋቾች ናቸው።

የ2016 የሊጉ አሸናፊ ሆነው ያጠናቀቁት ንግድ ባንኮች በቀጣዮቹ ቀናት ቡድናቸውን ለማጠናከር ወደ ዝውውሩ በስፋት እንደሚገቡ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ነገሌ አርሲ በረከት ግዛውን እና እንዳልካቸው ጥበቡን አስፈረመበአሰልጣኝ ቱሉ ደስታ የሚመሩት ነገሌ አርሲዎች አማካዩ በረከት ግዛውን በሁለት አመት ውል አስፈርመዋል።የቀድሞው የጂንካ ከተማ ፣...
31/07/2026

ነገሌ አርሲ በረከት ግዛውን እና እንዳልካቸው ጥበቡን አስፈረመ

በአሰልጣኝ ቱሉ ደስታ የሚመሩት ነገሌ አርሲዎች አማካዩ በረከት ግዛውን በሁለት አመት ውል አስፈርመዋል።

የቀድሞው የጂንካ ከተማ ፣ ሀላባ ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አማካይ ከሁለት አመት የአፄዎቹ ቆይታ በኋላ ማረፊያው ነገሌ አርሲ ሆኗል።

አዳዲስ ተጫዋቾች በማስፈረም የተጠመዱት ነገሌ አርሲዎች የቀድሞው የአርባ ምንጭ ከተማ እንዲሁም ደግሞ የተጠናቀቀውን የውድድር ዘመን በወልዋሎ ቆይታ የነበረውን እንዳልካቸውን ጥበቡን በሁለት አመት ውል ማስፈረማቸው ተረጋግጧል።

Address

Arbaminch
Arba Minch'
****

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Sport 343 ኢትዮ ስፖርት 343 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share