ኢትዮ ሶከር ዞን 4-5-1

ኢትዮ ሶከር ዞን 4-5-1 Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ኢትዮ ሶከር ዞን 4-5-1, Sports, Arbaminch gamo gofa, Arba Minch'.

የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ ለአዲሱ የውድድር ዘመን አዳዲስ ተጫዋቾችን አስፈረመየጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ በመጪው የ2019 የውድድር ዘመን ጠንካራና ተፎካካሪ ስብስብ በመገንባት ከፍተኛ ...
31/07/2026

የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ ለአዲሱ የውድድር ዘመን አዳዲስ ተጫዋቾችን አስፈረመ
የጋሞ ጨንቻ እግር ኳስ ክለብ በመጪው የ2019 የውድድር ዘመን ጠንካራና ተፎካካሪ ስብስብ በመገንባት ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ አዳዲስ ተጫዋቾችን አስፈርሟል።

ክለቡ ላለፉት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የቅጥርና የዝግጅት ሂደት ተከትሎ፣ የቡድኑን የማሸነፍ መንፈስና አጠቃላይ አቅም የሚያጎለብቱ ተጫዋቾች ወደ ስብስቡ ተቀላቅሏል።

​የክለቡ አመራሮች እንደገለጹት፤ የዘንድሮው የዝውውር እንቅስቃሴ የቡድኑን ጥንካሬና ድክመት በጥናት በመለየት እንዲሁም በቴክኒክ አሰልጣኞች ምክረ-ሀሳብ ላይ ተመስርቶ የተከናወነ ነው ብለዋል።

የዝውውሩ ዋና ዓላማም በመጪው የውድድር ዘመን በሊጉ መደበኛ ተሳታፊ ከመሆን አልፎ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ለከፍተኛ ደረጃዎችና ለዋንጫ በቁርጠኝነት የሚፎካከር ቡድን መገንባት እንደሆነ አስረድተዋል።

​አዳዲሶቹ ተጫዋቾች ከነባሮቹ ጋር በፍጥነት በመቀናጀት ለቡድኑ አዲስ ጉልበትና ፍጥነት እንደሚጨምሩ የታመነበት ሲሆን፣ ይህ አደረጃጀት በስፖርት ቤተሰቡና በደጋፊዎች ዘንድ ትልቅ ተስፋን የፈጠረ መሆኑንም ተመላክቷል።

በተጨማሪም ክለቡ ለተጫዋቾች አስፈላጊውን የስነ-ልቦና፣ የቴክኒክና የቁሳቁስ ድጋፍ በማሟላት ሙሉ አቅሙን አውጥቶ ለመፋለምና የደጋፊዎቹን ፍላጎት የሚያረካ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጁነቱን አረጋግጧል።

31/07/2026

ቼልሲ ምን አስቦ ነው ?
ኢትዮ ሶከር ዞን 4-5-1

አርባምንጭ ልማት ካፕ የዛሬ ጨዋቴ መርሀ ግብር በአንድ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሔድ በ 2ት ጨዋታዎች 6ት ነጥብን መያዝ የቻለው ኩልፎ 02 አጋፔ ጨንቻን 9:00 ላይ የሚያስተናግድ ይሆናል።የሚዲያ አ...
31/07/2026

አርባምንጭ ልማት ካፕ የዛሬ ጨዋቴ መርሀ ግብር በአንድ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሔድ በ 2ት ጨዋታዎች 6ት ነጥብን መያዝ የቻለው ኩልፎ 02 አጋፔ ጨንቻን 9:00 ላይ የሚያስተናግድ ይሆናል።

የሚዲያ አጋራቾቻን 👇
➧ ሳታ ኢንተርናሽናል አካዳሚ ፦ ለልጆቾ የተሻለ ወደፊት ሳታ ኢንተርናሽናል አካዳሚ ተቀዳሚ ምርጫ ያድርጉ 🙏

➧ ቤኪ የውበት ሳሎን እና ማሰልጠኛ ፦ ስለውበቷ እኛ አለንሎ

የአሰልጣኝ ተመስገን ዳና ጉዳይ በመጨረሻም ዕልባት አገኘከሀዋሳ ከተማ ጋር እንደሚቀጥሉ እና እንደማይቀጥሉ ማረጋገጫ ባለመገኘቱ ሲያወዛግብ የከረመው የአሰልጣኝ ተመስገን ዳና ጉዳይ በመጨረሻም ...
31/07/2026

የአሰልጣኝ ተመስገን ዳና ጉዳይ በመጨረሻም ዕልባት አገኘ

ከሀዋሳ ከተማ ጋር እንደሚቀጥሉ እና እንደማይቀጥሉ ማረጋገጫ ባለመገኘቱ ሲያወዛግብ የከረመው የአሰልጣኝ ተመስገን ዳና ጉዳይ በመጨረሻም ትላንት ሐሙስ ምሽት የክለቡ ቦርድ ባደረገው ዘለግ ያለ ስብሰባ የተለያዩ ሀሳቦች ከተነሱ በኋላ በመጨረሻም አሰልጣኝ ተመስገን ዳና ቀጣዩን አመት ሀዋሳ ከተማን እየመሩ እንዲቀጥሉ ወስኗል።

ቴዎድሮስ ታከለ ነኝ

አማኑኤል ኤርቦ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተመልሷልበአሁኑ ሰዓት የህክምና ምርመራውን ለማድረግ እየተጠባበቀ የሚገኘው አማኑኤል ኤርቦ በድጋሚ ፈረሰኞቹን መቀላቀል ችሏል። ከአርባምንጭ ከተማ ከተገኘ ...
30/07/2026

አማኑኤል ኤርቦ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተመልሷል

በአሁኑ ሰዓት የህክምና ምርመራውን ለማድረግ እየተጠባበቀ የሚገኘው አማኑኤል ኤርቦ በድጋሚ ፈረሰኞቹን መቀላቀል ችሏል። ከአርባምንጭ ከተማ ከተገኘ በኋላ ፣ በለገጣፎ ለገዳዲ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና የተጠናቀቀው አመት ደግሞ በኢትዮጵያ መድን ያሳለፈው ወጣቱ አጥቂ ከአንድ አመት በኋላ ወደ ቀድሞው ክለቡ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሁለት አመት ውል መመለሱ ተረጋግጧል።

ቴዎድሮስ ታከለ

በአርባምንጭ ከተማ እየካሔደ የሚገኘው የክረምት ውድድር የሆነው ልማት ካፕ ዛሬ ቀጥሎ ይካሔዳል። የጨዋታ ሰአቶችም ቀትር 7:00 እና ከሰአት 9:00 ላይ የሚደረጉ ይሆናል።የሚዲያ አጋራቾቻን ...
30/07/2026

በአርባምንጭ ከተማ እየካሔደ የሚገኘው የክረምት ውድድር የሆነው ልማት ካፕ ዛሬ ቀጥሎ ይካሔዳል። የጨዋታ ሰአቶችም ቀትር 7:00 እና ከሰአት 9:00 ላይ የሚደረጉ ይሆናል።

የሚዲያ አጋራቾቻን 👇
➧ ሳታ ኢንተርናሽናል አካዳሚ ፦ ለልጆቾ የተሻለ ወደፊት ሳታ ኢንተርናሽናል አካዳሚ ተቀዳሚ ምርጫ ያድርጉ 🙏

➧ ቤኪ የውበት ሳሎን እና ማሰልጠኛ ፦ ስለውበቷ እኛ አለንሎ

ፅዮን መርዕድ ወደ ፈረሰኞቹ ቤት አምርቷል!ከአርባምንጭ ከተማ ጋር በግሉ ጥሩ ጊዜን ያሳለፈው ግብ ጠባቂው መዳረሻው የፈረሰኞቹ ቤት ለመሆን ተቃርቧል።ፅዮን መርዕድ በአርባምንጭ ከተማ የግብ ጠ...
29/07/2026

ፅዮን መርዕድ ወደ ፈረሰኞቹ ቤት አምርቷል!

ከአርባምንጭ ከተማ ጋር በግሉ ጥሩ ጊዜን ያሳለፈው ግብ ጠባቂው መዳረሻው የፈረሰኞቹ ቤት ለመሆን ተቃርቧል።

ፅዮን መርዕድ በአርባምንጭ ከተማ የግብ ጠባቂነት ሕይወቱን መነሻ አድርጎ በመቀጠል በወላይታ ድቻ፣ በሀዋሳ ከተማ፣ በባህር ዳር ከተማ በድጋሚ ወደ ቀድሞ ክለቡ በመመለስ ያለፉትን ሁለት ዓመታት በአርባምንጭ ሲያገለግል ቆይቷል።።

ዘንድሮ የውል ጊዜው ያበቃው ፅዮን ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ለመጫወት መስማማቱን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

Via ፦ soccer Ethiopia

ፍፁም ጥላሁን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ተለያየፍፁም ጥላሁን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ውሉን ለማራዘም በደሞዝ ክፍያ ባለመስማማቱ ክለቡን መልቀቁ ተገልጿል
29/07/2026

ፍፁም ጥላሁን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ተለያየ

ፍፁም ጥላሁን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ውሉን ለማራዘም በደሞዝ ክፍያ ባለመስማማቱ ክለቡን መልቀቁ ተገልጿል

በአሰልጣኝ ታዲዮስ ተክሉ የሚመራው ቡድን አባላት ሲውዲን ላይ ጠፉከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ እግር ኳስ ተጫዋቾች ​በስዊድን ጎተንበርግ በተካሄደው የጎቲያ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር ላይ ...
29/07/2026

በአሰልጣኝ ታዲዮስ ተክሉ የሚመራው ቡድን አባላት ሲውዲን ላይ ጠፉ

ከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ እግር ኳስ ተጫዋቾች ​በስዊድን ጎተንበርግ በተካሄደው የጎቲያ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር ላይ የተሳተፉ ከ20 በላይ የሚሆኑ በቀድሞ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ሴቶች ቡድን ረዳት አሰሎጣኝ እና የንግድ ባንክ ወጣት ቡድን አሰልጣኝ ታዲዮስ ተክሉ መሪነት ያመሩት ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎችና የቡድን መሪዎች መጥፋታቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።

​ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁን የቦርከና ዘገባ ያመለክታል።

​የስዊድን የጠፉ ሰዎች የመርማሪ ክፍል ተወካይ ኤሊኖር ሃልዲን ግለሰቦቹ ወደ ኢትዮጵያ አለመመለሳቸውን አረጋግጫለሁ ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ በስዊድን የሚገኘው ኤምባሲ ስለ ኢትዮጵያዊያኑ መጥፋት ያሉት ነገር የለም።

"ኢትዮጵያ ቡና ከጠየቀኝ ቅድሚያ እሰጣለሁ" አቡበከር ናስር አቡበከር ናስር ከደቡብ አፍሪካ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን አረጋግጧል "ከየትኛውም ክለብ ጋር እስካሁን ድርድር አልጀመርኩም ማንም አላ...
29/07/2026

"ኢትዮጵያ ቡና ከጠየቀኝ ቅድሚያ እሰጣለሁ" አቡበከር ናስር

አቡበከር ናስር ከደቡብ አፍሪካ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን አረጋግጧል

"ከየትኛውም ክለብ ጋር እስካሁን ድርድር አልጀመርኩም ማንም አላነጋገረኝም በሚዲያ የሚገረው ሀሰት ነው

ኢትዮጵያ ቡናም ቢሆን እስካሁን አላናገረኝም ነገርግን ከደወሉ ቅድሚያ እሰጣቸዋለሁ ከገንዘብ ይልቅ ቡናን እና ቃሌን አስቀድማለሁ።"

"ለሌሎች ክለቦችም ክብር አለኝ" (misganaw tadese)

Address

Arbaminch Gamo Gofa
Arba Minch'

Telephone

+251916990065

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢትዮ ሶከር ዞን 4-5-1 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ኢትዮ ሶከር ዞን 4-5-1:

Shortcuts

Share

Category