03/02/2023
የደርቢውን ጨዋታ ትኬት ቁጥጥር !
እኛ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ማህበር ባለፉት አመታት ለታላቁ ክለብ በሜዳው በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የትኬት ቁጥጥር ስራ በማከናወን ተገቢውን ገቢ ክለቡ እንዲያገኝ የበኩሉን ተወጥቶ ነበር።
ሆኖም ግን በተለያየ ዓለም አቀፋዊ (ኮቪድ) እና ሀገራዊ ጉዳዮች ያለ ተመልካች የሚደረጉ ጨዋታዎች ከመብዛታቸው የተነሳ ለክለባችን የትኬት ቁጥጥር ስራ በሚፈለገው ደረጃ ማከናወን አልቻልንም ነበር።
ባለፉት 3 ወራት ግን የእኛ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ማህበር ባደረጋቸው ውይይቶች አዳማ ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎችን ክለባችን በተቻለ አቅም ከተመልካች የሚገኘውን የሜዳ ገቢ በሚገባ ያገኝ ዘንድ ስራዎችን ለመስራት ወስኗል።
በዚህም ዕለተ ቅዳሜ አዳማ ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ኢትዮጵያ ቡና የሚያደርገውን ጨዋታ የትኬት ቁጥጥር ከ15 በላይ አባላትን አሳትፎ የሚያከናውን ሲሆን ደጋፊዎች ለትኬት ቁጥጥር ኮሚቴዎች አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ እንጠይቃለን።
ድል ለቅዱስ ጊዮርጊስ!