31/05/2026
373
ኢኳዶሪያዊያኖቹ
ዊሊያን ፓቾ እና ፒየሮ ሂንካፒ!
ዕለተ እሁድ ግንቦት 23 /2018 ዓም የኢትዮ-አዲስ ስፖርት መሰናዶ ከቀኑ 6:00-7:00 በተወዳጁ ብስራት FM 101.1 ላይ አየር ላይ ይውላል።
የክለቦች ውድድር ቁንጮ የሆነው የአውሮፓ ቻምፕየንስ ሊግ በሀንጋሪ ቡዳፔስት በፑሽካሽ አሬና ስታድየም ተጠናቋል።
ፔዤ በድጋሜ የአውሮፓ ሀያልነቱን ክብር ያስጠበቀበት ድል ተጎናፅፏል።
መድፈኞቹ በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ አሸናፊ የሚሆኑበትን እድል ማሳካት አልቻሉም።
በዚህ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፓ ቻምፕየንስ ሊግ ፍፃሜ ሁለት ኢኳዶራዊያን በተቃራኒ ሆነው ተፋልመዋል።
ከፓሪስ በመቀጠል አሸናፊዋ ኢኳዶር ነበረች።
ዊልያን ፓቾ እና ፒየሮ ሂንካፒ
በትናንቱ ጨዋታ ላይ ኢኳዶርን ባኮሩት ወርቃማ ልጆቿ ዙሪያ ቆይታ እናደርጋለን።
እናንተስ የምሽቱ ጨዋታ እንዴት አያችሁት?
👉 የአርቴታ የጨዋታ አቀራረብ፣ ፣የተጨዋች ምርጫ እና ቅያሪ?
👉 የማጋሌሽ መለያ ምት ጉዳይ?
👉 ኤነሪኬ ለ 3ኛ ጊዜ የአውሮፓ ቻምፕየንስ ሊግ ዋንጫ አንስቷል።ታዲያ በታሪክ ከሰፈሩት ከቁንጮ አሰልጣኞች ዝርዝር እንዲገባ አያደርገውም?
በነዚህ እና በሌሎች ስፖርታዊ ጉዳዮች ላይ ሀሳባችሁን ፃፉልን።
- የሚሳተፉበትና የሚዝናኑበት