06/08/2026
ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ መድረክ ተጋጣሚዎቻቸውን አውቀዋል!!
⭐️ በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ ኢትዮጵያን የሚወክለው ሲዳማ ቡና በመጀመሪያው ዙር ማጣሪያ ከቻዱ ክለብ ኤግሎንስ ጋር የሚገናኝ ይሆናል።
-ሲዳማ ቡና ይህንን ጨዋታ በድል የሚወጣ ከሆነ፣ በሁለተኛው ዙር የሱዳኑ አል ሂላል እና የቡርንዲው አግል ኖይር አሸናፊ የሆነውን ክለብ የሚገጥም ይሆናል።
⭐️በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የሚሳተፈው ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ከሱዳኑ አል ሂላል አልሳሂል ጋር የተደለደለ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን የደርሶ መልስ ጨዋታ በሜዳው የሚያስተናግድ ይሆናል።
- ክለቡ ይህንን ዙር በድል ካጠናቀቀ ደግሞ ከዛንዚባሩ ኬኤምኬኤም እና ከሊቢያው አል አህሊ ትሪፖሊ አሸናፊ ጋር ለቀጣዩ ዙር ፍልሚያ እንደሚገናኝ ታውቋል።
👉 የሁለቱም ክለቦች የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ከነሐሴ 29 እስከ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ የሚከናወኑ ሲሆን፣ የመልስ ጨዋታዎች ደግሞ በአዲሱ ዓመት መጀመሪያ ከመስከረም 1 እስከ መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ እንደሚደረጉ የውድድሩ የጊዜ ሰሌዳ ያሳያል።