30/08/2026
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በታንዛንያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ማጣርያ ዝግጅቱን በዛሬው ዕለት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጀምሯል።
በዋናው ብሔራዊ ቡድን ዝግጅት ላይ ተካተው የነበሩትን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች በመጀመርያው የልምምድ መርሐ ግብር ላይ የተገኙ ሲሆን ከስብስቡ መካከል በጴጥሮስ ተሾመ ምትክ የኢትዮጵያ ቡናው የአብሥራ አስናቀ ተተክቷል።