10/06/2026
ሄይቲ "ማለያሽን ቀይሪ" ተባለች!
😱 ከ52 ዓመታት በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫ የተመለሰችው ሄይቲ ከ1974 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በምትሳተፍበት ትልቁ የእግር ኳስ መድረክ የመጀመሪያ የብሔራዊ ቡድኗን ማለያ ቀይሪ ተብላለች!
ዠ ግሎቦ (Ge Globo) እንደዘገበው፣ ፊፋ የሄይቲ ብሔራዊ ቡድን ማሊያ የፖለቲካ መልዕክት የያዘ ነው በሚል እንዲቀየር ጠይቋል። በሄይቲ ብሔራዊ ቡድን ማሊያ ላይ የሀገሪቱ የነፃነት ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ የሚወሰደውና ከፈረንሳይ ጋር የተደረገውን ታሪካዊ ጦርነት የሚያሳየው 'የቨርቲየሬስ' ጦርነት (Battle of Vertières) ስዕላዊ መግለጫ ሰፍሮ ይገኛል።
በመጀመሪያ ላይ አንዳንድ ወገኖች በማሊያው ላይ ያለው ንድፍ የፖላንድን ባንዲራ የሚያሳይ መስሏቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህም ፖላንድ ሄይቲ ለነፃነቷ ባደረገችው ትግል ወቅት ላበረከተችው ድጋፍ የተሰጠ ክብር እንደሆነ አስበው ነበር። ነገር ግን ማሊያው ላይ ያለው ምስል በትክክል የሚያመለክተው የሄይቲን የመጀመሪያዋን ብሔራዊ ባንዲራ ነው።
ፊፋ አሁን ባለው መመሪያ መሰረት የዓለም ዋንጫው ከመጀመሩ በፊት ማሊያው በአስቸኳይ እንዲቀየር አዟል።