02/11/2025
በቀን 23/02/2081 ዓ.ም.በቻይና በተካሄደው የማራቶን ውደድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸነፉ።
በቻይና በቤጂንግ እና ሆንዙ በተካሄደው የማራቶን ውድድር በሁለቱም ፆታዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል።
በሆንዙ የማራቶን ውድድር በሴቶች አትሌት ሩቲ አጋ በ2:24:29 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን አሸንፋለች።
በወንዶች አትሌት ጫሉ ደሶ በ2:11:15 በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።
በተመሳሳይ በቤጂንግ በተካሄደው የማራቶን ውድድር በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2:08:10 በመግባት ሲያሸንፍ÷ አትሌት ደሳለኝ ግርማ ሁለተኛ ወጥቷል።
በሴቶች አትሌት አንቻሉ ደሴ በ2:26:06 በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ÷ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ቁፍቱ ጣሂር ሦስተኛ ወጥታለች።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!