02/06/2026
ኤቨርተን ኢሊማን ንዲያዬን ለማቆየት እየታገለ ይገኛል
********************
ኤቨርተን አጥቂው ኢሊማን ንዲያዬ የቀረበለትን አዲስ የውል ማራዘሚያ ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ ተጫዋቹን በክለቡ የማቆየት ከባድ ፈተና ገጥሞታል።
በክለቡ እና በተጫዋቹ ወኪሎች መካከል የሚደረገው ንግግር ከዓመቱ መጀመሪያ ጀምሮ እየተካሄደ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ስምምነት ላይ መድረስ አልተቻለም።
ዘ አትሌቲክ ይዞት የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው ለስምምነቱ መዘግየት አንዱና ዋነኛው ምክንያት በውሉ ላይ እንዲካተት የተጠየቀው የውል ማፍረሻ ክፍያ ሲሆን፣ ኤቨርተን በማንኛውም የወደፊት ዝውውር ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖረው ይፈልጋል።
በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳታፊ የሆኑ ክለቦች፣ ተጫዋቹን ለማስፈረም ጥረት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ነገር ግን ኤቨርተን የ26 ዓመቱን ተጫዋች ለማቆየት ቆርጦ ተነስቷል።
ንዲያዬ በአሁኑ ውሉ ላይ አሁንም ሶስት ዓመት የሚቀረው ሲሆን፣ በክለቡ ውስጥ ካሉ እጅግ ውድ ተጫዋቾች አንዱ ተደርጎ ይወሰዳል።
የቀድሞው የሼፊልድ ዩናይትድ እና የማርሴይ አጥቂ ባለፈው የውድድር ዘመን 6 የፕሪሚየር ሊግ ግቦችን አስቆጥሯል።
በዓለም ዋንጫው ላይ ለሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ድንቅ ብቃቱን የሚያሳይ ከሆነ ይበልጥ የብዙዎችን ትኩረትን ይስባል ተብሎ ይጠበቃል።
በእሱባለው ተሾመ