05/08/2026
⚠️⚠️ጠቃሚ ምክር!
ከአቡ ሁረይራ (🤎) ተይዞ፡ ረሱል (🤎) እንዲህ ብለዋል፦
﴿اتَّقِ الْمَحَارِمَ تَكُنْ أَعْبَدَ النَّاسِ، وَارْضَ بِمَا قَسَمَ اللَّهُ لَكَ تَكُنْ أَغْنَى النَّاسِ، وَأَحْسِنْ إِلَى جَارِكَ تَكُنْ مُؤْمِنًا، وَأَحِبَّ لِلنَّاسِ مَا تُحِبُّ لِنَفْسِكَ تَكُنْ مُسْلِمًا، وَلَا تُكْثِرِ الضَّحِكَ ؛ فَإِنَّ كَثْرَةَ الضَّحِكِ تُمِيتُ الْقَلْبَ﴾
“ከተከለከሉ (ሀራም) ከሆኑ ነገሮች ተጠንቀቅ (ታቀብ) ከሰዎች በተሻለ አላህን አምላኪ (አቢድ) ትሆናለህ። አላህ በሰጠህ ልክ ተብቃቅተህ ኑር በኑሮው የተብቃቃና ደስተኛ ትሆናለህ። ለጎረቤትህ መልካምን የሚውል (በጥሩ የሚኗኗር ሁን) ትክክለኛ አማኝ (ሙዕሚን) ትሆናለህ። ለራስህ (ለነፍስህ) የምትወደውን ለሌሎች ሰዎችም ውደድ ትክክለኛ ሙስሊም ትሆናለህ። ሳቅ አታብዛ፤ ሳቅ ማብዛት ልብን ያደርቃል (ይገድላል)።”
📚 ቲርሚዚ ዘግበውታል፡ 2305