Ethio athletics center

Ethio athletics center the ways of athletics idea

Happy birthday 🎂🎂🎂🎂
13/06/2026

Happy birthday 🎂🎂🎂🎂

አትሌት አዲሱ ይሁኔ በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ አሸነፈ ሰኔ 3/2018 ዓ.ም በኦስሎ 2026 ዳይመንድ ሊግ ውድድር በወንዶች 5000 ሜትር አትሌት አዲሱ ይሁኔ በአስደናቂ የአጨራረስ ብቃት አሸነፈ...
10/06/2026

አትሌት አዲሱ ይሁኔ በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ አሸነፈ

ሰኔ 3/2018 ዓ.ም

በኦስሎ 2026 ዳይመንድ ሊግ ውድድር በወንዶች 5000 ሜትር አትሌት አዲሱ ይሁኔ በአስደናቂ የአጨራረስ ብቃት አሸነፈ::

አትሌት አዲሱ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 12:47.62 የወሰደበት ሲሆን ያስመዘገበው የዓመቱ ፈጣን ስዓት ነው።

በውድድሩ የተካፈሉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መዝገቡ ስሜ 7ኛ ፣አትሌት ቢንያም መሃሪ 9ኛ ደረጃ ይዘው ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

አትሌት አዲሱ ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደው ሺያመን ዳይመንድ ሊግ በ5ሺ ሜትር ማሸነፉን የሚታወስ ነው።@

በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ አትሌት ፍረወይኒ ሀይሉ አሸነፈች ።ሰኔ 3/2018 ዓ.ምበኦስሎ ዳይመንድ ሊግ በሴቶች 3000 ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀዋል ።በውድድሩ አት...
10/06/2026

በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ አትሌት ፍረወይኒ ሀይሉ አሸነፈች ።

ሰኔ 3/2018 ዓ.ም

በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ በሴቶች 3000 ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀዋል ።

በውድድሩ አትሌት ፍረወይኒ ሀይሉ 8:24.22 በመግባት የወቅቱ ፈጣን ስዓት በማስመዝገብ በአንደኝነት አሸንፋለች ።

አትሌት ልቅና አምባው 8:25.15 በመግባት 2ኛ፣አትሌት ሰናይት ጌታቸው 8:25.85 የግል ምርጥ ስዓቷን በማስመዝገብ 3ኛ እና አትሌት ሀዊ አበራ 8:27.18 በመግባትና የግል ምርጥ ስዓቷን በማስመዝገብ 4ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቋል ።

09/06/2026
ለመገናኛ ብዙሃን !የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር እሁድ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም በድምቀት ለማካሄድ ዝግጅቱን ጨርሰዋል ።በዚህም መሰረት ዓርብ 28...
03/06/2026

ለመገናኛ ብዙሃን !

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር እሁድ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም በድምቀት ለማካሄድ ዝግጅቱን ጨርሰዋል ።

በዚህም መሰረት ዓርብ 28/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ላይ በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ይሰጣል

ስለሆነም በቦታው እና በሰዓቱ ተገኝታችሁ መረጃውን ለስፖርት ቤተሰብ እንድታደርሱን በአክብሮት እንጠይቃለን ።

ሰበር ዜና!!      በማድሪድ  በተካሔደዉ የ10 ኪሎ ሜትር  ውድድር ብሩንዳዊው አትሌት ሮድሪግ ክዊዘርላ  26.01 በመሮጥ የአለም ፈጣን ሰአት በሆነ ሰአት አሸነፈ።
31/05/2026

ሰበር ዜና!!

በማድሪድ በተካሔደዉ የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር ብሩንዳዊው አትሌት ሮድሪግ ክዊዘርላ 26.01 በመሮጥ የአለም ፈጣን ሰአት በሆነ ሰአት አሸነፈ።

Goal
30/05/2026

Goal

በዓለም አትሌቲክስ ሽልማት (World Athletics Awards) አመራረጡ ላይ ትልቅ ለውጥ ተደረገ።ኖቬምበር 29 በሞናኮ ከሚካሄደው የ2026 የሽልማት ስነ-ስርዓት በፊት፣ የዓመቱ ምርጥ አ...
30/05/2026

በዓለም አትሌቲክስ ሽልማት (World Athletics Awards) አመራረጡ ላይ ትልቅ ለውጥ ተደረገ።

ኖቬምበር 29 በሞናኮ ከሚካሄደው የ2026 የሽልማት ስነ-ስርዓት በፊት፣ የዓመቱ ምርጥ አትሌት ሽልማትን ለመምረጥ የሚያስችል አዲስ የድምፅ አሰጣጥ ስርዓት ይፋ ሆኗል።

'ዋና ዋና ለውጦች'
የአትሌቶች አመራረጥ በትራክ፣ በሜዳ እና በጎዳና ላይ ውድድሮች ተብለው በተናጠል መሸለም ቀርቷል።
በምትኩ 10 ወንዶች እና 10 ሴቶች በአጠቃላይ ታጭተው፣ በመጨረሻም እያንዳንዳቸው ወደ 3 እጩዎች ይቀራሉ።

'ድምፅ አሰጣጥ'
አሸናፊዎቹ የሚለዩት አራት የተለያዩ ክፍሎች ናቸው።
እያንዳንዳቸው 25% ድምፅ አላቸው።

ድምጽ የሚሰጡ አካሎች
* የWorld Athletics (Subscribers)
* በ2026 የዓለም አትሌቲክስ የሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ላይ የተሳተፉ አትሌቶች፣
* እውቅና ያላቸው ጋዜጠኞች (እዚህ ጋር እኔ አለሁበት🤞
* የዓለም አትሌቲክስ ቤተሰቦች (የአትሌቲክስ ፕሬዝዳንት፣ የውድድር አዘጋጆች፣ የፌዴሬሽን አባል ፕሬዝዳንቶችና ሌሎችም) ናቸው።

በመድረኩ ላይ ሌሎች ሽልማቶችም አሉ እነሱም ተስፋ ሰጪ (Rising Star)፣ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ፣ የፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ሽልማት እና የዓመቱ ምርጥ ክስተት አትሌት ሽልማትን ያካትታሉ።

*የዓመቱ ምርጥ ክስተት" (Moment of the Year) ሽልማት፦
ይህ ደግሞ አዲስ የመወዳደሪያ ዘርፍ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ በደጋፊዎች እጅ ነው!
በዓመቱ ውስጥ እጅግ አስደሳች ለነበረው የተለየ ክስተት ደጋፊዎች በማህበራዊ ሚዲያ በቀጥታ ድምፅ መስጠት ይችላሉ። ምናልባት ዮሚፍ ቀጄልቻ እዚህ ለመመረጥ ሰፊ ዕድል ይኖረዋል ብዬ እገምታለሁ።

ማስጠንቀቂያ
(Moment of the Year) የአማርኛ ትርጉም፦
"የዓመቱ ምርጥ ክስተት" ብዬ ወደ አማርኛ ተርጉሜዋለሁ፤ የተሻለ ነገር ካለ መቀየር መብታችሁ ነው።

ከኢትዮጲያ ለዕጩነት ማንን እንጠብቅ
*ትዕግስት አሰፋ
*ዮሚፍ ቀጀልቻ
* ፎቴን ተስፋዬ
*ገመዶ ደደፎ (አሰልጣኝ)
* ስለሺ ስህን (ፕሬዚደንት)

Congratulations
19/05/2026

Congratulations

Address

Addis Ababa

Telephone

+251913790640

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio athletics center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio athletics center:

Share