Ethio athletics center

Ethio athletics center the ways of athletics idea

አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ የብራስልስ ዳይመንድ ሊግ 5,000 ሜትር አሸናፊ ሆነች🇪🇹🇪🇹🇪🇹ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም1 አትሌት ፍሬወይኒ የ5,000 ሜትር ውድድሩን 14:35.20 በሆነ ጊዜ በማጠና...
04/09/2026

አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ የብራስልስ ዳይመንድ ሊግ 5,000 ሜትር አሸናፊ ሆነች🇪🇹🇪🇹🇪🇹

ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
1 አትሌት ፍሬወይኒ የ5,000 ሜትር ውድድሩን 14:35.20 በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ በአንደኝነት ማሸነፍ ችላለች።🇪🇹

2 አትሌት ልቅና አምባው በ14:36.31 ሁለተኛ ስትሆን፣ 🇪🇹

3 አትሌት ሰናይት ጌታቸው ደግሞ በ14:37.09 ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።🇪🇹

30/08/2026
በግማሽ ማራቶን ውድድር አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ አቀባበል ተደረገለትአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን...
26/08/2026

በግማሽ ማራቶን ውድድር አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር በወንዶች አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ እና በሴቶች የውድድሩን አዲስ የቦታ ክብረወሰን በማስመዝገብ ያሸነፈችው አትሌት ፎቴን ተስፋይ አቀባበል ተደረገላቸው።

አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 56:51 በሆነ ጊዜ በመግባት በዩጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ ተይዞ የነበረውን 57:20 የዓለም ክብረወሰን በግማሽ ማራቶን በማሻሻል አዲሱን የዓለም ምርጥ ሰዓት ማስመዝገቡ ይታወሳል።

በሴቶች ውድድር ደግሞ አትሌት ፎቴን ተስፋይ 1:03:57 በሆነ ጊዜ በመግባት የውድድሩን የቦታ ክብረወሰን በማሻሻል በአንደኝነት ማሸነፏ አይዘነጋም።

ሁለቱ አትሌቶች አዲስ አበባ ሲገቡ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህንን ጨምሮ ሌሎች የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በፌዴራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ አጃቢነት ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

በአኖካ ዞን 5 ውድድር   ኢትዮጵያ  በአትሌቲክስ ሦስት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች።በውድድሩ ሁለተኛ ቀን ውሎ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አስደናቂ ብቃት በማሳየት 3 የወርቅ እና 1 የብር ሜዳሊያ ...
26/08/2026

በአኖካ ዞን 5 ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ሦስት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች።

በውድድሩ ሁለተኛ ቀን ውሎ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አስደናቂ ብቃት በማሳየት 3 የወርቅ እና 1 የብር ሜዳሊያ አሸንፈዋል።

በ3 ሺህ ሜትር ሴቶች ዮርዳኖስ ፀጋብ በቀዳሚነት በማጠናቀቅ አሸንፋለች።

አትሌቷ በኦሪገን ከ20 አመት በታች በ3000ሜ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ማሸንፏ ይታወቃል።

በ800 ሜትር ነፃነት ሰለሞን በቀዳሚነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ ስታሸንፍ አትሌት ነይማን ነርሲንግ በሴቶች 5 ኪሎ ሜትር እርምጃ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች።

በ1500 ሜትር ወንዶች ዋቢ ዊርድ የብር ሜዳሊያ አሸንፏል።
China abdi

Obbo Tammasgeen guddina dhallootaa fi dinagdee hawaasaa irratti hojiiwwan gurguddoo hojjechaa jiraanHojiiwwan isaan adda...
26/08/2026

Obbo Tammasgeen guddina dhallootaa fi dinagdee hawaasaa irratti hojiiwwan gurguddoo hojjechaa jiraan
Hojiiwwan isaan adda dureedhaan irratti hirmaatan keessaa gurguddoon:
Atileetikisii fi Kubbaa Milaa Dagasuudhaaf godinaalee Oromiyaa hunda keessatti dargaggoota simachuu, deeggaru fi jajjabeessu irratti
Dhalloota gara fuulduraa ijaaruuf sektera barnootaa irratti deeggarsa deebii maleeyyii fi pirojektoota garaa garaa deggaruu.
Gumaacha fi aarsaa isaan godhaa jiraniif beekamtii kennuun dargaggoota fi qooda-fudhattoota biroos kan jajjabeessudha.

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በጎዳና ላይ ውድድሮች ድል አስመዝግቧል ሐምሌ 20/2018 ዓ.ምየኢትዮጵያ አትሌቶች በጣሊያን፣ በኮሎምቢያ እና በብራዚል በተካሄዱ ዓለም አቀፍ የጎዳና ሩጫ ውድድሮች ድ...
27/07/2026

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በጎዳና ላይ ውድድሮች ድል አስመዝግቧል

ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ አትሌቶች በጣሊያን፣ በኮሎምቢያ እና በብራዚል በተካሄዱ ዓለም አቀፍ የጎዳና ሩጫ ውድድሮች ድንቅ ውጤቶችን አስመዝግቧል ።

በጣሊያን በተካሄደው የ11 ኪሎ ሜትር ጂሮ ዴል ካስቴልቡኦኖ ውድድር የኦሎምፒክ የማራቶን ሻምፒዮኑ አትሌት ታምራት ቶላ 34:26 በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ የአንደኝነት ድልን ተቀዳጅቷል።

በርቀቱ የተሳተፈው ጣልያናዊው አትሌት የማነብርሃን ክሪፖ ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል ።

በኮሎምቢያ ቦጎታ ግማሽ ማራቶን፣አትሌት በረከት ነጋ ሁለተኛ ደረጃን ሲያስመዘግብ፣አትሌት መላል ስዩም በሴቶች ዘርፍ አሸናፊ ሆናለች።

አትሌት አይናለም ደስታ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቃለች።

በብራዚል ሳኦ ፓውሎ ግማሽ ማራቶን፣አትሌት አለሙ ባልቻ በወንዶች ሲያሸንፍ፣አትሌት ድንቅነህ ግርማ ሁለተኛ ደረጃን አግኝቷል።

በሴቶች ደግሞ አትሌት ትዕግሥት ግርማ አሸናፊ ስትሆን፣አትሌት ሰብለ ታደሰ ሶስተኛ ደረጃን ውድድሯን አጠናቃለች ።

መሪር ሀዘን!!😭😭😭 አትሌት ራምቦ ዱርሳይ የ110መሰናክል የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌት የሆነዉ በደረሰበት ድንገተኛ  አደጋ በትላንትናዉ ዕለት ህይወቱ አልፏል። በአትሌት ራምቦ ዱረሳይ ህልፈት ...
12/07/2026

መሪር ሀዘን!!😭😭😭

አትሌት ራምቦ ዱርሳይ የ110መሰናክል የኢትዮ ኤሌክትሪክ አትሌት የሆነዉ በደረሰበት ድንገተኛ አደጋ በትላንትናዉ ዕለት ህይወቱ አልፏል።

በአትሌት ራምቦ ዱረሳይ ህልፈት የተሰማኝ ሀዘን እጅግ ጥልቅ ነው። ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹ እና ለመላው የአትሌቲክስ ቤተሰብ ከልብ መጽናናትን እመኛለሁ።

ነፍስ ይማር!!😭😭
Via China abdi

የኦሮሚያ ፖሊስ ስፖርት ክለብ በቅርብ ጊዜያት በሀገር ውስጥና በአለም አቀፍ መድረኮች ላይ እያስመዘገበ ያለው ተከታታይ ድል በአመራሩ፣ በአሰልጣኞችና በአትሌቶች መካከል ባለው ጠንካራ ቅንጅትና...
12/07/2026

የኦሮሚያ ፖሊስ ስፖርት ክለብ በቅርብ ጊዜያት በሀገር ውስጥና በአለም አቀፍ መድረኮች ላይ እያስመዘገበ ያለው ተከታታይ ድል በአመራሩ፣ በአሰልጣኞችና በአትሌቶች መካከል ባለው ጠንካራ ቅንጅትና ስራ የመጣ መሆኑን በግልጽ ያሳያል። ክለቡ በተለይም በማራቶን እና በረጅም ርቀት ውድድሮች እንዲሁም በትራኩና ድሮዎች ላይ እያሳየ ያለው የበላይነት የሚደነቅ ነው።
የክለቡን ስኬታማ ጉዞ የሚያሳዩ ዋና ዋና ነጥቦች፦
የ ዛሬ ሐምሌ 05/11/2018 ድል፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባዘጋጀው የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ በሁለቱም ጾታዎች (በወንዶችም በሴቶችም) አንደኛ በመውጣት ክለቡ ያለውን የላቀ ብቃት በድጋሚ አስመስክሯል።
ለምሳለ፦ ክለቡ በነቀምቴ፣ በሀዋሳ፣ በአዲስ አበባ እንዲሁም በአለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ ጭምር በደመቀ ሁኔታ ማሸነፍ መቻሉ በየደረጃው ያለውን ጠንካራ ዝግጅት ያሳያል።
የአመራርና የቴክኒክ ቅንጅት፦ ከኦሮሚያ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች ጀምሮ እስከ ታችኛው የአሰልጣኞች ቡድን ድረስ ያለው የተቀናጀ ድጋፍ እና እቅድ ለአትሌቶቹ የስነ-ልቦና እና የቴክኒክ ጥንካሬ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

08/07/2026

Address

Addis Ababa

Telephone

+251913790640

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio athletics center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio athletics center:

Shortcuts

Share