Saint George Sport Club Families - የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፓርት ክለብ ቤተሰቦች

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • Saint George Sport Club Families - የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፓርት ክለብ ቤተሰቦች

Saint George Sport Club Families - የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፓርት ክለብ ቤተሰቦች ይህ ገጽ የእኛ የፈረሰኞቹ ነው! እኛ ጊዮርጊስ አለ በተባለበት ቦታ ሁሉ የምንገኝ!
ሳንጃው ፈረሰኞቹ ሼባው አርበኛው አራዶቹ ሼባው Sanjaw Shebaw
(1)

09/05/2026

የቀድሞው አመራር ትቶልን የሄደው በእቅድ የማይመራ ዝብርቅርቅ ያለውን አሰራር ማስተካከል ራሱ ሌላ ስራ ነው፥፥ አሁን እንደለመድኩት የምተቸው ሰው የለም፥፥ መተቸት ሱስህ ነው ትሉኝ የለ፥፥ ስተችም እኮ በምክንያት ነበር፥፥ ወደ ሱሴ ለመመለስ ቢያንስ ክለቡ በቦርድ እንደገና መዋቀር አለበት፥፥ ይህ ነገር እስከመቸ እንደሚቆይ አላውቅም መረጃውም የለኝም፥፥ ቢያንስ ኮሚቴው ግልጽነት ቢኖረው ደስ ይለኛል፥፥ ገና ለገና ያለፈውን ቦርድ ማንሳት ስለቻልንም ግባችን ያ የሆነ ይመስል ዝም ጭጭ ተብሏል ይልቅ ኮሚቴው ሀላፊነት እስካለበት ድረስ አንዳንድ ነገሮችን ግልጽ ማድረግ ቢችሉ ደስ ይለኛል፥፥ ተሰብስቦ ትሪቡን መዘፍዘፍ ብቻ ትርጉም የለውም፥

ይልቅ ሳንጃው ሰው አለው ስንል ትክክል እንደነበርን እያሳዩን ያሉት ጀማልን ማመስገን እፈልጋለሁ፥

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የተጨዋች ዝውውር እገዳ በጊዜያዊነት አነሳቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ተጥሎበት የነበረው የተጨዋቾች ዝውው...
09/05/2026

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የተጨዋች ዝውውር እገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ተጥሎበት የነበረው የተጨዋቾች ዝውውር እግድ በጊዜያዊነት ተነስቷል፡፡

ክለባችን የቅጣት መክፈያ ገንዘቡን ከአቶ ጀማል አህመድ በስጦታ ባገኘ በሁለት ቀናት ውስጥ ለአራቱ ከሳሽ ተጫዋቾች ሙሉ ክፍያ ከቅጣት ጋር ከፍሎ ቢያጠናቅቅም ሞሀመድ ላሚን ኮኔ ለፊፋ ያስገባው የባንክ ሂሳብ ቁጥር ትክክል ባለመሆኑ ምክንያት ገንዘቡ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተመላሽ ተደርጓል፡፡ ተጨዋቹ እስከ አሁን ባለመላኩ ምክንያትም እገዳው ሳይነሳ ሳምንታት ቆይተዋል፡፡

ክለባችንም የተጠየቀውን ሁሉንም ህጋዊ ሁኔታዎች ማሟላቱንና የኮኔ ገንዘብም ያልተከፈለው በተጨዋቾ የራሱ ችግር መሆኑን ገልፆ ለፊፋ አቤቱታ አቅርቧል፡፡ ፊፋ የቅዱስ ጊዮርጊስን ጥያቄ በመቀበል ኮኔ ትክክለኛውን የባንክ ሂሳብ ቁጥሩን እንዲልክና ክለባችንም የኮኔን ክፍያ እስከሚከፍል ድረስ ተጥሎበት የነበረው እግድ በጊዜያዊነት እንዲነሳ ወስኗል፡፡ የኮኔ ክፍያ በቀጣይ ጥቂት ቀናት ሲጠናቀቅ ክለባችን በቋሚነት ከእግድ ነጻ እንደሚሆን ታውቋል፡፡

የዝውውር እገዳው በጊዜያዊነት መነሳቱን ተከትሎ ክለባችን ለውድድሩ የሚሆኑትን የሀገር ውስጥ እና የውጪ ተጨዋቾች ለማስፈረም ወደ ገበያ የሚገባ ይሆናል፡፡

ክለቡ በእነዚህ አራት ተጫዋቾች ቀርቦበት የነበረውን ከፍተኛ ክፍያ በመፈጸም ክለቡን ከእገዳ ነጻ እንዲሆን ያደረጉት የክለባችን ዋነኛ ደጋፊ እና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አህመድ ናቸው፡፡

የጥላፎቅ የሁለት ሁለት ዘመናት ወግነጭ የሚባል ማሊያ ሳይታወቅና ከታወቀ በኃላበዚሁ ከቀጠልን የሆነ ግዜ ሪያል ማድሪድን እናስንቃለን 😙
03/05/2026

የጥላፎቅ የሁለት ሁለት ዘመናት ወግ
ነጭ የሚባል ማሊያ ሳይታወቅና ከታወቀ በኃላ

በዚሁ ከቀጠልን የሆነ ግዜ ሪያል ማድሪድን እናስንቃለን 😙

በሰሞነኛው የአደጋገፋችን ሁኔታ ላይ ሀሳቦች እዚህም እዚያም መነሳት መጀመራቸው ይበል የሚያሰኝ መሆኑን እየገለፅኩ፣ እኔም የበኩሌን ጥቂት ነገር ለማለት ወደድኩ . . .ቀደም ሲል የክለባችን ...
03/05/2026

በሰሞነኛው የአደጋገፋችን ሁኔታ ላይ ሀሳቦች እዚህም እዚያም መነሳት መጀመራቸው ይበል የሚያሰኝ መሆኑን እየገለፅኩ፣ እኔም የበኩሌን ጥቂት ነገር ለማለት ወደድኩ . . .

ቀደም ሲል የክለባችን ልዩ ምልክት ተደርጎ ይወሰዱ ከነበሩ ነገሮች መሃል አንደኛው ልዩ የሆነው የአደጋገፍ ስታይላችን እንደሆነ ይታወቃል፣ ይሁን እንጂ የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ከረጅም ጊዜያት በኋላ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሱ በኋላ ግን ይህ ማንነታችን አብሮን እንደሌለ ማንም የሚያስተውለው እውነታ ሆኗል!

በደርቢው ጨዋታ በዋነኛው ባላንጣችን ደጋፊዎች የድጋፍ ድምፅ ተውጠን ጨዋታው መጠናቀቁ የሚታወስ ሲሆን፣ ይባስ ብሎም በሲዳማ ቡናው ጨዋታ ባለሜዳው ክለብ ማን እንደነበረ ለመለየት በሚከብድ ሁኔታ ከሜዳው ውጪ በሚጫወተው ቡድን ደጋፊዎች የድጋፍ ማዕበል ብልጫ ተወስዶብናል፤ ​ይህንን ክስተት፣ በአንድ ክለብ የልብ ደጋፊዎች መካከል መቃቃርና በጎራ መከፋፈል ሲኖርና ይህንን ቅሬታቸውንም ወደ ስታዲየም ይዘው ሲመጡ ድጋፉ ምን ሊመስል እንደሚችል አይነተኛ አመላካች ማስረጃ አድርጎ ማቅረብ ይቻላል።

​ከምንም በላይ "የጥላ ፎቅ" መደብዘዝ በአፋጣኝ መፍትሄ ያሻዋል! ይህ ቦታ የታላቁ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች የድጋፍ አንቀሳቃሽ "ሞተር" መሆኑ ቀርቶ የሴራና የጠብ መናኸሪያ እየሆነ ነው። አንዱ ጎራ የሚዘምረውን ሌላኛው ጎራ በማጣጣል ወይም በዝምታ ወይም በመቃወም ተጫዋቾቻችን ከኛ ከደጋፊዎቻቸው ሊያገኙ የሚገባቸውን ንፁህ የሞራል ድጋፍ እንዳያገኙ እያደረገ ነው፤ ​ለቁጥር ቀላል የማይባል ደጋፊም በተፈጠረው የደጋፊዎች ክፍፍል ምክንያት ስታዲየም መምጣት ሲያቆም፣ የተወሰነው ደጋፊም የቦታ ለውጥ በማድረግ ኳሱን ብቻ አይቶ መውጣቱን መፍትሄ አድርጎ ተቀምጧል። የድጋፉ ሁኔታም ፍፁም ቅዱስ ጊዮርጊስን በማይመጥኑ ዝማሬዎች፣ ጭፈራዎችና ስነ-ቃሎች ተተክቷል።

ይኼ ነገር እስከ መቼ በዚህ መልኩ ይቀጥላል?
​መልሱ ቀላል ባይሆንም ግልፅ ነው፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፋና ወጊና ምልክት እንደመሆኑ መጠን፣ የውስጥ ሰላሙ መታወክ ለሌሎች ክለቦችም መጥፎ አርአያነትን እንደሚፈጥር ልንረዳ ይገባል፤ በዚሁ መንገድ መቀጠላችንም፣ መጨረሻው የክለቡን ታላቅነት ማርከስና ተወዳዳሪነቱን ማጥፋትም ጭምር እንደሆነ በሚገባ ልንገነዘብ ይገባል!

በመሆኑም በደጋፊዎች መካከል የተፈጠረውን መከፋፈልና መቃቃር በእውነተኛ እርቅ እልባት መስጠት ጊዜ ሊሰጠው የማይገባው ስራ ሊሆን ይገባል፤ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን የክለባችንን ስም፣ ታሪክና ማንነት ፍፁም በማይመጥን በዚሁ አሳዛኝ መንገድ እንዳንቀጥል ያሰጋል!

ከ2008 በሗላ በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ አዲስ ነገረ ወደ ስታዲየም መጣ። እነዛ 20 ናቸው 30 ናቸው የሚሉትን የተቃራኒ ክለብ ደጋፊዎች እና ጋዜጠኞችን ኩም ያደረገ ሪቮሊውሽን ተፈጠረ። በ...
03/05/2026

ከ2008 በሗላ በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ አዲስ ነገረ ወደ ስታዲየም መጣ። እነዛ 20 ናቸው 30 ናቸው የሚሉትን የተቃራኒ ክለብ ደጋፊዎች እና ጋዜጠኞችን ኩም ያደረገ ሪቮሊውሽን ተፈጠረ። በተለያየ መንገድ ብትንትን ብሎ የነበረው የኢትዮጵያ እግርኳስ ድጋፍ ወደ የሚያምር ወደ የሚያስደነግጥ የህብረት የቅብብሎሽ ድጋፍ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ቀየሩት። ለዚህ ለውጥ ብዙ ዝግጅት በህብረት በመተጋገዝ በመተባበር ቢደረግም ዋናው መሪ ደሞ ኢዮባ ሳንጃው አበባ ነች። ብዙ ነገር ቀየረች እዮባ ብዙ አዳዲስ የሚያማምሩ የድጋፍ ስልቶችን ይዛ መጣች፣ በአንዴ የስታዲየም ድባብ ከተራ ነቆራና ብትንትን ካሉ ጩኸቶች ወደ ሚያምር ውብ ወደሆነ ድባብና ድጋፍ ተቀየረ። የተቃራኒ ክለብ ደጋፊዎች ካቅማቸው በላይ ያላሰቡት ነገር ስለገጠማቸው በድንጋጤ ኩም አሉ፣ በአድናቆት እስኪፈዙ ጋዜጠኞች ጊዜ ሰተው እስኪዘግቡ እና እስኪቀኑ ድረስ ተደነቁ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከማንም ጋር ሲጫወት ስታዲየሞች መሙላት ጀመሩ ከ 2008 በፊት ሚስማር ላይ በድፍረት ማሊያ ለብሰው የሚገቡት 4 ልጆች ብቻ ነበሩ (ተስፍቲ , እዮብ ,ቴዲ እና ብራቮ ብራቮ ሳንጃው) ብቻ ነበሩ። ከ 2008 በሗላ ግን ሚስማር በቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ ተወረሰ። አትደነቅም ያኔ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በተለያየ ምክንያት ከሜዳ የራቀው ደጋፊ ወደ ስታዲየም እዲመለስ አዳዲስ ደጋፊዎችም አስገራሚ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎችን የስታድየም የድጋፍ ውበት በማየት ወደ ስታዲየም በአስደናቂ ሁኔታ በጣም በብዛት መምጣት መትመም ጀመሩ።

ሌላው አስገራሚ ነገር ከተቃራኒ ክለብ ደጋፊዎች ያንን ክለብ በመተው ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊነት በብዛት መቀየር ጀመሩ፣ በየ ሀገሩ በየከተማው በየሰፈሩ የቅዱስ ጊዮርጊስ ማሊያን በሚያረጉ ወጣቶች በየቀነኑ መተራመስ ጀመረ። በእውነት ይሔን ማየት ህልም ነበር። ደስታዬ ወደር አልነበረውም አስቡት እስኪ ቀስ እያሉ እኮ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊን እየሸረሸሩ እያጠፉት ነበር።

በፊት የቅዱስ ጊዮርጊስን ማሊያ ያረገ ሰው መንገድ ላይ ማየት ብርቅ ነበር፣ በተለይ ከ 2003 እስከ 2007 ድረስ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊን ከሜዳ የማጥፋት ነገር ቴክኒካሊ ሲሰራ ነበር። እድሜ ለጋዜጠኞች ሚድያው የአንድ ክለብ እስኪመስል ድረስ ቅዱስ ጊዮርጊስን አገለሉት፣ ስለእኛ ሚድያ ላይ መስማት ብርቅ ነበር። በተጨማሪም ሙስና የሚል ቅጽል ስም በመስጠት በአሉባልታና በተለያየ መንገድ ደጋፊውን አሸማቀው እያጠፉብን ነበር። ነገር ግን አልተሳካላቸው።

ከ 2008 በሗላ የተጀመረው የደጋፊዎች ወደ ስታዲየም የመመለስ ሪቮሊውሽን ከሚያማምር የስታዲየም የቅብብሎሽ ድጋፍ ጋር ደጋፊው ወደሜዳ ተመለሰ አስገራሚ ነው፣ ሙሉ እታዲየም በቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በቁጥጥር ስር ዋለ። 20 ናቸው ብለው ሲጨፍሩብን የነበሩ አፈሩ ፣ እነሱ የሚቀመጡበትን ሚስማር ተራን ጨምሮ ቀኝ ጥላፎቃቸው ሁሉንም መቀመቻቸውን ወረስነው፣ ፈነጨንበት፣ ጨፈርንበት 2009 አይወራ የደጋፊው ድባብ እየጨመረ መጣ፣ ፍላሽ ላይቶች መጠቀም ጀመርን፣ የኛ የድጋፍ ስልቶችም ሌላ ክለቦች መኮረጅ መዝረፍ ጀመሩ አይፈረድባቸውም የሚያምር ነገር አይተው እዴት ይለፉት። የሚገርመው ነገር እነ እንትና 2010 አስፈርቷቸው ስለነበር 2009 ክረምት ድጋፍ ጥናት ብለው ተሰብስበው ሜክሲኮ ቡና እና ሻይ ማጥናት ጀመሩ። ነገር ግን የፈሩት አልቀረም 2010 የቅዱስ ጊዮርጊስ አዲሱ ትውልድ በገፍ ወደ ስታድየም መትመም ጀመረ። ከዚህ በላይ ምን ደስታ አለ በአዲሱ ትውልድ ልበ ሙሉ ማንንም የማይሰማ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ የኢትዮጵያ እግርኳስን ተቆጣጠረ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ እደ አሸን ፈላ በእውነት በጣም አስደሳች ነው ጥሩ መስመር ላይ ባለንበት ኮሮና የሚባል ምቀኛ በሽታ መጣና እስታዲየሞችን ወና አረጋቸው ኮሮናም ካለፈ በሗላ በከተማችን ጨዋታዎችን ማረግ አልቻልንም ነገር ግን አሁን ላይ ጨዋታዎች ለደጋፊ ክፍት እየሆኑ ስላሉ የድጋፍ ነገር አሳሳቢ ነው ክለባችንን ቅዱስ ጊዮርጊስ ለመደገፍ ከመሯሯጥ አዲስ ነገር ከማምጣት ይልቅ ደጋፊውን ወደ እስቴድዮም ከመመለስ ይልቅ ካታንጋ ጥላፎቅ እየተባባሉ አዱን ከፍ አንዱን ዝቅ ለማረግ በሚመስል መልኩ መንቀሳቀስ ይታያል ይህ ተገቢ አይደለም ሁሉም ቦታዎች የቅዱስ ጊዮርጊስ ቦታዎች ናቸው ሁሉም መድመቅ አለበት የአንዱ ቦታ መፍዘዝ የቅዱስ ጊዮርጊስ መፍዘዝ ነው ተራ ነገሮች ቀርተው ደጋፊው በሙሉ ሀይይሉ ወደ እስታዲየም የሚመለስበትን ነገር በማሰብ ከወዲሁ ለ 2019 ዝግጅት ማድረግ አለብን በእዮባ ሳንጃው የተሰሩ መዝሙሮች በበቂ ሁኔታ እስታድየም ውስጥ እየተዘመሩ አይደለም በግል ተጫዋች እና አሰልጣኝን ከቡዱኑ ነጥለን ከሚጨፈር ሙሉ ቡዱናችንን መስዋት ከፍሏል ስለዚህ ሁሉንም የሚያበረታቱ መዝሙሮቻችንን ብንጠቀም መልካም ነው አስጨፋሪዎችም አዳዲስ ነገር እስኪፈጠር ይሔን አርጉ በህብረት መዝሙሮቻችን ከፍብለው ይዘመሩ ጣፋጭ ናቸው።

በመጨረሻም አዳዲስ ፊት አቅም ያላቸው ግጥም መፍጠር የሚችሉ አዳዲስ ነገር መፍጠር የሚችሉ አስጨፋሪዎች መጨመር አለባቸው ለ 2019 ካሁኑ ስራዎች መሰራት አለባቸው ያ ውብ ድጋፍ መመለስ አለበት ሞዛይኮች መሰራት አለባቸው እስታዲየም ነፍስ እዲዘራ ውብ እዲሆን ማድረግ አለብን✌️❤
ምንጊዜም ቅዱስ ጊዮርጊስ ✌️❤
#ሼር #ቅዱስ #ጊዮርጊስ

"ስምንት ትልልቅ ክለቦችን አሰልጥኛለሁ ፥ አራት ብሄራዊ ቡድኖችንም አሰልጥኛለሁ ፥ ክለብ ክለብ ነው ፥ ብሄራዊ ቡድንም ብሄራዊ ቡድን ነው፡፡ነገር ግን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤቴ ነው፡፡ኢትዮጵያም ...
02/05/2026

"ስምንት ትልልቅ ክለቦችን አሰልጥኛለሁ ፥ አራት ብሄራዊ ቡድኖችንም አሰልጥኛለሁ ፥ ክለብ ክለብ ነው ፥ ብሄራዊ ቡድንም ብሄራዊ ቡድን ነው፡፡ነገር ግን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤቴ ነው፡፡ኢትዮጵያም ቤቴ ናት፡፡በአፍሪካ ካሉት አራቱ ትልልቅ ሊጎች ማለትም ደቡብ አፍሪካ ፥ ግብጽ ፥ አልጄሪያ እና ሞሮኮ በሶስቱ አሰልጥኛለሁ ፥ መናገር የምችለው አንድ ነገር ኢትዮጵያ ፥ ኢትዮጵያውያን ፥ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ደጋፊዎች ፥ አሰልጣኞቹ እና ተጫዋቾቹ እኔ እኔን እንድሆን አድርገውኛል፡፡በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያን ሁሌም በልዩ አይን ነው የማያት፡፡ኢትዮጵያ አንድ ተራ ሀገር አይደለችም፡፡ኢትዮጵያ ቤቴ ናት፡፡"

🇪🇹

💚💛❤️

ሚቾ ከOBN ጋር በነበራቸው ቆይታ ከተናገሩት

የታሪክ አደራ.. የችግር ጊዜ ኩራት .. የቅዱስ ጊዮርጊስ እውነተኛ ማንነት የሆኑትን ልጆቻችንን ደጋግመን ልናመሰግን ግድ ይላል። በዚህ ፎቶ ላይ የሚታየው የአንድ ቡድን ስብስብ ብቻ አይደለም...
02/05/2026

የታሪክ አደራ.. የችግር ጊዜ ኩራት .. የቅዱስ ጊዮርጊስ እውነተኛ ማንነት የሆኑትን ልጆቻችንን ደጋግመን ልናመሰግን ግድ ይላል።

በዚህ ፎቶ ላይ የሚታየው የአንድ ቡድን ስብስብ ብቻ አይደለም። የጽናት፣ የፍቅር፣ እና የትጋት ህያው ምስክርነት ነው። ዛሬ የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን የገጠመው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስብስብ እግር ኳስ ከገንዘብ በላይ መሆኑን ያሳየን ነው። ዘንድሮ በአገራችን እግር ኳስ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል። ብዙ ክለቦች በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ብሮችን አፍስሰው የዝውውር ገበያውን አጥለቅልቀው، ቡድን ለመገንባት ጥረዋል። ይህ ምንም መጥፎ ነገር የለውም፣ የዘመኑ እግር ኳስ ባህሪ ነው።
ነገር ግን የእኛ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዘንድሮ ከሌሎቹ የተለየ መንገድ መርጧል..ወይም ደግሞ ሁኔታዎች አስገድደውታል። ክለባችን በገንዘብ እጥረት ውስጥ እያለፈ እንደሆነ ሁላችንም እናውቃለን። ይሁን እንጂ ይህ ችግር በሩን እንዲዘጋው ወይም በውድድሩ ላይ ተስፋ እንዲቆርጥ አላደረገውም። ይልቁንስ ወደ ዋናው እሴቱ، ወደ መጀመሪያው ምንጩ እንዲመለስ አድርጎታል። ያ ምንጭ ደግሞ የክለባችን ልጆች ናቸው!.
በዚህ ፎቶ ላይ ካሉት ቋሚ 11 ተጫዋቾች ውስጥ ስድስቱ የክለባችን የታዳጊዎች ቡድን ያፈራቸው፣ በቅዱስ ጊዮርጊስ ማሊያ ያደጉ፣ የክለቡን መንፈስ የሚያውቁ ልጆች ናቸው። ብዙዎች ከውጪ የመጡ ኮከቦችን ሲፈልጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን በእራሱ አትክልት ውስጥ የበቀሉትን አበቦች እየተንከባከበ ነው።

ይህ ለየት ያለ ስሜት ይሰጣል። እነዚህ ልጆች ለቡድኑ የሚጫወቱት ለደሞዝ ወይም ለዝና ብቻ አይደለም። ክለቡን ስለሚወዱት፣ የእግር ኳስ “ሀ ሁ” በተማሩበት ሜዳ ላይ ለመውደቅ እና ለመነሳት ስለሚፈልጉ ነው። በቡድኑ ውስጥ ያለውን አስቸጋሪ ጊዜ የሚያልፉት በገንዘብ ሳይሆን፣ በኩራት፣ በታማኝነት፣ እና በአብሮነት መንፈስ ነው።.
ይህ ታሪክ የእኛ ኩራት ነው። ገንዘብ ሊገዛው የማይችል፣ በችግር ውስጥ የሚፈጠር ጥንካሬ ነው። ዛሬ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን እነዚህ ልጆች በሜዳ ላይ የሚያሳዩት ጥረት የድል ያህል ነው። እነሱ የቅዱስ ጊዮርጊስን ታሪክ አዲስ ምዕራፍ እየጻፉ ነው።
ለእነዚህ ልጆች፣ ለዚህ ቡድን እና ለእውነተኛው የቅዱስ ጊዮርጊስ መንፈስ ምንጊዜም ድጋፋችን አይለይም። በችግር ውስጥ የበቀሉ፣ በኩራት የቆሙ ጊዮርጊሳዊያን ናቸውና ደጋግመን ብናመሰግናቸው ያንስባቸዋል እንጂ አይበዛባቸውም።

እናመሰግናለን ልጆቻችን

Habtamu Viva Sanjaw

ሰርቪያዊው ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ መጥተዋልከፈረሰኞቹ ጋር አምስት የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ያነሱት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ወደ ቀድሞው ክለባቸው ተመልሰዋል።በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ከታዩ ድንቅ ...
01/05/2026

ሰርቪያዊው ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ መጥተዋል

ከፈረሰኞቹ ጋር አምስት የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ያነሱት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ወደ ቀድሞው ክለባቸው ተመልሰዋል።

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ከታዩ ድንቅ የውጪ ዜጋ አሰልጣኞች መካከል አንዱ መሆን የቻሉት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ሰርዲ ሚሊት ሚቾ ወደ ቀድሞው ክለባቸው ቅዱስ ጊዮርጊስ በአማካሪነት መመለሳቸውን አውቀናል። አስራ ሁለት ክለቦችን እና አምስት ሀገራት ደግሞ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ መሰልጠን የቻሉት አሰልጣኙ እንደ ኦርላንዶ ፓይሬት ፣ ያንጋ አፍሪካ ፣ አልሂላል እና ዛማሌክ ያሉ የአፍሪካ ስመ ጥር ክለቦችን ማሰልጠን ቢችሉም እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ስኬታማ የሆኑበት ቡድን የለም ከ1997 እስከ 2002 ክለቡን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ በፈረሰኞቹ ቤት አምስት የፕሪምየር ሊግ ዋንጫዎችን ያነሱ ሲሆን አንድ የጥሎ ማለፍ ዋንጫን ከክለቡ ጋር ማንሳት ችለዋል።

ትላንት በአዲስ አበባ ስታዲየም የፕሪምየር ሊጉን ጨዋታዎች ሲመለከቱ የነበሩት እና በቅርቡ በአልጄሪያ ሊግ ከሚወዳደረ ኢ ኤስ ስቲፍ ጋር በመለያየት ለዕረፍት ትዳር ወዳገኙባችፈት ኢትዮጵያ የመጡት አሰልጣኝ ሚቾ እስከ ውድድር ዘመኑ ፍፃሜ ድረስ አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝን በሜዳ እና ከሜዳ ውጪ በጨዋታ እና ከጨዋታ ውጪ የቀድሞው ክለባቸውን እያገዙ አመቱን እንደሚቆዩ የሰማን ሲሆን እንዳገሁት መረጃ ከሆነ ግን ከሌሎች የአፍሪካ ክለቦች ጋር ንግግር ላይ የሚገኙት አሰልጣኙ የቅዱስ ጊዮርጊስን የፋይናንስ ስርዓት መሻሻልን ተከትሎ ጥሩ ክፍያን የሚያገኙ ከሆነ ቀጣዩን አመት በክለቡ የዋና አሰልጣኝነት ሚና ልናያቸው እንደምንችልም ማወቅ ችያለሁ።
ሀትሪክ

ሰርቢያዊው አሰልጣኝ ሰርዲዮቪች ሚሉቲን (ሚቾ)  አርባምንጭ ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እያደረጉት ባሉት ጨዋታ አዲስ አበባ ስታዲየም ታድመው ጨዋታውን ተከታትለዋል። ከ1997 እስከ 20...
30/04/2026

ሰርቢያዊው አሰልጣኝ ሰርዲዮቪች ሚሉቲን (ሚቾ) አርባምንጭ ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እያደረጉት ባሉት ጨዋታ አዲስ አበባ ስታዲየም ታድመው ጨዋታውን ተከታትለዋል።

ከ1997 እስከ 2002 ዓ.ም የቅዱስ ጊዮርጊስ የአምስት ዓመታት ቆይታቸው
5 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ፣
3 የአሸናፊዎች አሸናፊ እና
1 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ አሸናፊ የነበሩት እኚህ የ56 ዓመት አሰልጣኝ ከአልጄርያው ክለብ ሰቲፍ ከተለያዩ በኋላ ዕረፍት ላይ እንዳሉ ይታወቃል።

 አቶ ጀማል አህመድ ለክለባችን ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ገቢ ካደረጉ 6 ቀናት ተቆጥረዋል! ይህ ገንዘብ ለ4የውጭ ዜጋ ተጨዋቾች ባልተከፈለ ደሞዝ ምክንያት የተጣለውን የፊፋ እገዳ ለማስነሳት ...
30/04/2026



አቶ ጀማል አህመድ ለክለባችን ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ገቢ ካደረጉ 6 ቀናት ተቆጥረዋል! ይህ ገንዘብ ለ4የውጭ ዜጋ ተጨዋቾች ባልተከፈለ ደሞዝ ምክንያት የተጣለውን የፊፋ እገዳ ለማስነሳት እንደሚውል ተገልፆ ነበር! ነገር ግን እስካሁኗ ሰአት ድረስ ይህ ክፍያ አልተፈፀመም!

ለምን??????

ደሞዝ ካልተከፈላቸው 4 ተጨዋቾች የ 3ቱ ተጨዋቾች ከዋናው ክፍያ በተጨማሪ እየቆጠረ ያለው ወለድ 1ሚሊየን ብር ደርሷል (ወለዱ ብቻ!!)

ስለዚህ ፅ/ቤቱ፣ ኮሚቴው እና የሚመለከታቸው አካላት ምንድነው እየሰሩ ያሉት???

ቅዱስ ጊዮርጊስ ክፍያው ተከፍሎ እገዳው ተነስቶለት አሁን ያለውን ቡድን ለማጠናከር ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ Free Agent የሆኑ ተጨዋቾችን አስፈርሞ ይህን አመት ያለስጋት የሚያጠናቅቅበት እንዲሁም ለቀጣይ አመት የሚሆኑ ተጨዋቾችን በመመልመል ካልተዘጋጀ ነገሮች ቀላል እንደማይሆኑ ግልፅ ነው።

ፋይናንስ ሲታጣ የሚቸገር ሲገኝም ለታለመለት አላማ በስርዓትና በፍጥነት በትክክለኛ አሰራር የማይውል ከሆነ አሁንም ከፋይናንስ ውጪ ክለቡ ውስጥ ያለው የተጨመላለቀ አሰራር መቀጠሉን ጉልህ ማሳያ ይሆናል!

The Clock Is Ticking ነቃ በሉ!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Saint George Sport Club Families - የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፓርት ክለብ ቤተሰቦች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category