Times መረጃ

Times መረጃ ወቅታዊ ሀገራዊ እና አለማቀፋዊ መረጃዎችን የሚያገኙበት ገፅ

የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፓርቲያቸው ብልጽግና የተለየ አቋም በመያዝ እና በፓርላማው ይህንኑ ካንፀባረቁ በኋላ ወደ አሜሪካ በመሰደድ ተቀጥረው በመስራት ላይ መሆናቸ...
26/08/2026

የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፓርቲያቸው ብልጽግና የተለየ አቋም በመያዝ እና በፓርላማው ይህንኑ ካንፀባረቁ በኋላ ወደ አሜሪካ በመሰደድ ተቀጥረው በመስራት ላይ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ እርሳቸው ያሉበት የስራ ዘርፍ በቪዲዮ ተቀርፆ መሰራጨቱን ተከትሎ አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት አቶ ገዱ "ራሴን በራሴ ለማስተዳደር መቻሌ ኩራትና ክብር እንጂ ዝቅጠት አይሰማኝም" ብለዋል ።

በተለይ እንደ አንድ የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣንና ኃላፊነት ላይ እንደነበረ ሰው፣ ከስልጣናቸው በኋላ የተስተካከለ ኑሮ ሊያኖራቸው የሚችል ገንዘብ ባለመያዛቸው ይቆጫቸው እንደሆነ የተጠየቁት አቶ ገዱ "እኔ በነበረኝ የስልጣን ዘመን የማምንበትን ዓላማ ለማሳካት ነው የሰራሁት እንጂ ከህዝብ ሀብት ላይ የግል ኑሮዬን ለማደላደል አስቤ አላውቅም" ብለዋል። ይህም አሁን ንጹህ ህሊና ኖሮኝ እንድኖር ረድቶኛል ሲሉ ገልጸዋል።
አሁን ላይም ሰው በተለይ ኢትዮጵያውያን ትኩረት ሊያደርጉበት የሚገባው የእኔ የስራ ጉዳይ ሳይሆን በሀገሪቱ የሰላም ጉዳይ ነው ሲሉ "ሰው መጨነቅና አጀንዳ ማድረግ ያለበት እኔ በምሰራው ስራ ሳይሆን ሀገር ቤት በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ስላለው ህዝብ መሆን አለበት" ያሉት አቶ ገዱ ትልቁ ጉዳይ መሆን ያለበት ሀገራችን እንዴት ወደ ሰላም እንመልሳት የሚለው ነው ብለዋል።

ስራዬም ተረጋግጬ እንዳስብ፣ የቤት ኪራዬን እና ሌሎች ክፍያዎቼንም እንድከፍል የሚረዳኝ ነው ያሉት አቶ ገዱ በተለይ ከህዝቡ ለተቀበሉት ገንቢ አስተያየትና ላገኙት አክብሮት ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ምስጋናቸው የላቀ መሆኑን ገልጸዋል።
የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

የፌደራል መንግስቱ የቀረቡ ቅድመ ሁኔታዎችየአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ እና የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴንጉ ኦባሳንጆ በአሜሪካ፣ በአፍሪካ ህብረት እና በአውሮፓ ህብረት በሚደገፍ ...
25/08/2026

የፌደራል መንግስቱ የቀረቡ ቅድመ ሁኔታዎች
የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ እና የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴንጉ ኦባሳንጆ በአሜሪካ፣ በአፍሪካ ህብረት እና በአውሮፓ ህብረት በሚደገፍ የሰላም ጥረት ወደ መቀሌ በመጓዝ ከዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል ጋር ተወያይተው ተመልሰዋል። የኦባሳንጆ የመቀሌ ጉዞ ዋና ዓላማ በህወሃት እና በፌደራል መንግስቱ መካከል ዳግም ያገረሸው ውጥረት ወደ ከፋ ግጭት እንዳያመራ ለማሸማገል እንደሆነ ታውቋል።
ይህ የኦባሳንጆ የሰላም ጥረት በፌደራል መንግስቱ እውቅና የተከናወነ ሲሆን የፌደራል መንግስቱ ለድርድር ለመቀመጥ ሶስት ዋና ዋና ቅድመ ሁኔታዎችን በኦባሳንጆ በኩል ለህውሃት ሰዎች ማቅረቡ ተገልጿል።
የመጀመሪያው ቅድመ ሁኔታ የፌደራል መንግስቱ የስራ ዘመናቸውን ለአንድ ዓመት አራዝሞላቸው የነበሩትና በአሁኑ ወቅት በመቀሌ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በቁም እስር ላይ ናቸው የተባሉት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጄነራል ታደሰ ወረደ ወደ ስልጣናቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ ነው። ሁለተኛው ቅድመ ሁኔታ ደግሞ ህወሃት ከፋኖ ከኤርትራ መንግስት እና ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የመሰረተውንና “ፅምዶ” የተሰኘውን ህብረት እንዲያቋርጥ የሚጠይቅ ነው። ይህ ስብስብ በቅርቡ አመራሮቹን መምረጡ የሚታወስ ሲሆን፣ ዓላማውም የብልጽግና ፓርቲ የሚመራውን መንግስት ከስልጣን ማስወገድ እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል።
ሶስተኛው እና የመጨረሻው የፌደራል መንግስቱ ቅድመ ሁኔታ ህወሃት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በማክበር ታጣቂዎቹን በዲ.ዲ.አር (DDR) መርሃ ግብር መሰረት ትጥቅ እንዲያስፈታ የሚል ነው።
በሌላ በኩል ህወሃት ባወጣው መግለጫ መሰል ቅድመ ሁኔታዎችን ያቀረበ ሲሆን፤ ከነዚህም መካከል የወልቃይት እና የራያ አካባቢዎች ወደ ትግራይ ክልል እንዲመለሱ፣ የፌደራል መንግስቱ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲያቆም እና በክልሉ ላይ የተጣለው የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲነሳ የሚሉ ይገኙበታል።
የአሜሪካ ኤምባሲ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መረጃ፤ ይህ የኦባሳንጆ የሰላም ጥረት በአሜሪካ እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ሙሉ ድጋፍ ያለው መሆኑን አረጋግጧል።
የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ በኢትዮጵያውያን የሰላም አስከባሪዎች ላይ የተፈፀመውን ጥቃት አወገዙ።በደቡብ ሱዳን ጆንግሌ ግዛት በማይታወቁ ታጣቂዎች በተሰነዘረ የደፈጣ ጥቃት ሁለት ...
25/08/2026

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ በኢትዮጵያውያን የሰላም አስከባሪዎች ላይ የተፈፀመውን ጥቃት አወገዙ።
በደቡብ ሱዳን ጆንግሌ ግዛት በማይታወቁ ታጣቂዎች በተሰነዘረ የደፈጣ ጥቃት ሁለት ኢትዮጵያውያን የሰላም አስከባሪዎች መገደላቸውንና ሰባት ሌሎች ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።
የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በደቡብ ሱዳን የተመድ የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ (UNMISS) አባላት ላይ የተፈጸመውን ይህንን ጥቃት በፅኑ አውግዘዋል። ጥቃቱ የተፈጸመው ሰላም አስከባሪዎቹ በመደበኛ የጥበቃ ሥራ ላይ እያሉ በማይታወቁ የታጠቁ ግለሰቦች መሆኑን ገልፀዋል።

ዋና ጸሐፊው በደረሰው ሕይወት መጥፋት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸው፣ ለሟች ቤተሰቦች፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት መፅናናትን ተመኝተዋል። በተጨማሪም በጉዳቱ የቆሰሉት ሰባት ወታደሮች በፍጥነትና በሙሉ ጤንነት እንዲያገግሙ ያላቸውን ምኞት አስተላልፈዋል።
አንቶኒዮ ጉተሬዝ አክለውም፣ በተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕግጋትን በከፍተኛ ሁኔታ የሚጥሱ መሆናቸውን አስታውሰዋል። ድርጊቱም እንደ ጦርነት ወንጀል ሊቆጠር እንደሚችልም አሳስበዋል።
የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በኢትዮጵያ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ ላይ ያላቸውን ስጋት ገለጹ።የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃ...
09/08/2026

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በኢትዮጵያ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ ላይ ያላቸውን ስጋት ገለጹ።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረኢየሱስ በዛሬው ዕለት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ያለው የትጥቅ ግጭት እንዲቆምና በአስቸኳይ ወደ ሰላማዊ አማራጭ እንዲመጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ባሰፈሩት ጽሁፍ "ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ሰላም እንጂ ተጨማሪ ጦርነት አይደለም" በማለት አገሪቱ ያለችበትን አስከፊ የጸጥታ ሁኔታ አመልክተዋል። ዶክተር ቴዎድሮስ በዝርዝር በገለጹት ነጥብ በአማራ ክልል ለሦስት ዓመታት የዘለቀው የትጥቅ ግጭት የበርካታ ዜጎችን ሕይወት መቅጠፉን ገልጸዋል። በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል ያለው ደም መፋሰስ መቀጠሉን በትግራይ ክልል ዳግም ወደ ግልጽ ጦርነት የመግባት ስጋት መኖሩን እንዲሁም የአፋር እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በግጭትና በዓመጽ ውስጥ መቆየታቸውን በአጽንኦት ጠቁመዋል።
"በቃ!" በማለት ጠንከር ያለ መልዕክት ያስተላለፉት ዋና ዳይሬክተሩ የፌዴራል መንግሥቱም ሆነ የክልል መሪዎች ከጦር መሣሪያ ይልቅ ለውይይት ቅድሚያ እንዲሰጡና እውነተኛ ፖለቲካዊ መፍትሔዎችን እንዲፈልጉ አሳስበዋል።
ጦርነት በዜጎች ላይ የሚያስከትለውን ሰብዓዊ ቀውስ የገለጹት ዶክተር ቴዎድሮስ ግጭት የሞት ፣ የውድመት ፣ የመፈናቀል እና የከፋ እጦት ምንጭ መሆኑን አስገንዝበዋል። በመጨረሻም "ኢትዮጵያውያን ከዚህ የተሻለ ሰላማዊ ሕይወት ይገባቸዋል" ሲሉ ንግግራቸውን ደምድመዋል።

የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

ብልጽግና ፓርቲ ከፓርቲው አቅጣጫ ውጭ በሚንቀሳቀሱ አባላቱ ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ከተጀመረ ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን በሂደቱም በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ የተራ...
28/07/2026

ብልጽግና ፓርቲ ከፓርቲው አቅጣጫ ውጭ በሚንቀሳቀሱ አባላቱ ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀ
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ከተጀመረ ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን በሂደቱም በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ የተራራቁ አቋሞች እየተንፀባረቁ ይገኛሉ። ገዥው ብልጽግና ፓርቲ በጉባኤው እየተሳተፉ የሚገኙ አባላቱ ፓርቲው ቀደም ሲል በአዳማ ስብሰባ የሰጣቸውን አቅጣጫ ተከትለው እንዲንቀሳቀሱና ከዚህ መስመር በወጡ አመራሮች ላይ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተገልጿል።
በተለይ የአዲስ አበባን የሕግ ሁኔታ በተመለከተ፣ የፓርቲውን ይፋዊ አቋም ወደ ጎን በመተው "አዲስ አበባ የኦሮሚያ አካል መሆን አለባት" የሚል አቋም የያዙ አመራሮች ላይ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ደርሷቸዋል። እነዚህ አመራሮች ከአቋማቸው ካልተመለሱ "ከኃላፊነት እስከ መነሳት" የሚደርስ እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚችል በግልጽ እንደተነገራቸው ታውቋል።
ከዚህ በተጨማሪም፣ በሰንደቅ ዓላማ ቀለማት ላይ ለውጥ እንዲደረግ የሚጠይቁ ሀሳቦች በምክክሩ ወቅት ከቀረቡ፣ የፓርቲው አባላት "ምክክሩን አቋርጦ እስከመውጣት" የሚደርስ ጽኑ ተቃውሞ እንዲያሳዩ መመሪያ ተሰጥቷቸዋል። ፓርቲው እነዚህንና መሰል መመሪያዎችን ለአባላቱ እያስተላለፈ የሚገኘው በጉባኤው የዕረፍት ቀናትና ተመካካሪዎች ባሉባቸው ማደሪያ ቦታዎች በሚያዘጋጃቸው አነስተኛ ስብሰባዎች መሆኑ ተገልጿል።

የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

በአዳማ ከሰሞኑ አከራካሪ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ መካሄዱ ታወቀበፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አዳም ፋራህ የተመራውና ከየክልሉ የተወጣጡ ከ300 በላይ አ...
13/07/2026

በአዳማ ከሰሞኑ አከራካሪ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ መካሄዱ ታወቀ
በፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አዳም ፋራህ የተመራውና ከየክልሉ የተወጣጡ ከ300 በላይ አባላት የተሳተፉበት በዚህ ስብሰባ ላይ፤ ፓርቲው ለሀገራዊ ምክክሩ እንደ አቋም የያዛቸውና ሊተገበሩ ይገባል ያላቸው አጀንዳዎች ቀርበው ሰፊ ክርክር ተካሂዶባቸዋል። በተለይም ለሀገራዊ ምክክሩ የተዘጋጁና አከራካሪ የሆኑ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሃሳቦች በሁለት የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የቀረቡ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል "የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እስከ መገንጠል" ከሚለው ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ውስጥ "...እስከ መገንጠል" የሚለው ሐረግ እንዲሰረዝ የሚለው ይገኝበታል። በተጨማሪም የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ያለው "ልዩ ጥቅም" የሚለው ድንጋጌ ቀርቶ ወደ "የጋራ ጥቅም" እንዲቀየር የሚል ሃሳብ ቀርቧል።
አሁን ያለው የክልሎች አወቃቀር ለሀገር አንድነት ስጋት ነው ተብሎ ስለሚታመን፣ ክልሎች በቋንቋና በማንነት ሳይሆን በጂኦግራፊያዊ አቀማመጥና በኢኮኖሚ ትስስር ላይ ተመስርተው እንዲዋቀሩ የሚል አጀንዳ በዋነኝነት ቀርቧል። ከዚህ ጋር ተያይዞም አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ራሳቸውን የቻሉ ክልሎች እንዲሆኑና በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውስጥ ውክልና እንዲኖራቸው የሚሉ ነጥቦች ተነስተዋል። በመሬት ባለቤትነት ረገድም መሬት የመንግሥትና የሕዝብ ብቻ መሆኑ ቀርቶ የግል ባለቤትነትን እንዲያካትት፣ ይህም መሬትን እንደ አስፈላጊነቱ ለመሸጥና ለመለወጥ እንዲሁም ለኢንቨስተሮች ዋስትና ለመስጠት እንዲያስችል ማሻሻያ እንዲደረግ ተጠይቋል።
ከቀረቡት አጀንዳዎች መካከል በተለይ "ክልሎች በማንነት ሳይሆን በጂኦግራፊና በኢኮኖሚ ይዋቀሩ" የሚለውን ሃሳብና የኦሮሚያ "ልዩ ጥቅም" ቀርቶ "የጋራ ጥቅም" ይሁን የሚሉትን ነጥቦች የኦሮሚያ ክልል አመራሮች በጽኑ ተቃውመውታል። በሌላ በኩል በሕገ-መንግሥቱ መግቢያ ላይ የሚገኘው "እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች" የሚለው ሐረግ በ"እኛ ሕብረብሔራዊ የኢትዮጵያ ሕዝቦች" በሚል እንዲተካ ፓርቲው አቋም መያዙ ተገልጿል። ይህ ከሰኔ 23 እስከ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ የተካሄደው ስብሰባ መረጃዎች ባለፈው ሳምንት በስፋት ሲሰራጩ መቆየታቸው ይታወሳል።
የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

የኤርትራ መንግስት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ በፓርላማ ቀርበው ለሰጡት ማብራሪያ እና በተለይ ከኤርትራ (ሻዕቢያ)፣ ከሕወሓት እና ከሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ላነሷቸው ...
07/07/2026

የኤርትራ መንግስት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ በፓርላማ ቀርበው ለሰጡት ማብራሪያ እና በተለይ ከኤርትራ (ሻዕቢያ)፣ ከሕወሓት እና ከሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ላነሷቸው ነጥቦች በማስታወቂያ ሚኒስቴሩ በኩል ፈጣንና ጠንከር ያለ ምላሽ ሰጥቷል። ሁለቱ ወገኖች በቀጠናው ሰላምና በጎረቤት ሀገራት ጣልቃ ገብነት ዙሪያ እርስ በርሳቸው ተቃራኒ የሆኑ ክሶችን ሰንዝረዋል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በፓርላማ ንግግራቸው በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወጣቶችን በጉልበት እያፈሱ ለሱዳን ጦርነት "እየሸጡ" መሆኑን ገልጸዋል። "የትግራይ ወጣቶች በማያውቁት ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ህይወታቸውን እያጡ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ድርጊት የህዝቡን መከራ የሚያባብስ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
በተቃራኒው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ለሱዳን ግጭት መባባስ ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት ራሱ ነው ሲል ገልጿል። ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈርና ማሰልጠኛ በመስጠት በቀጥታ በጦርነቱ ውስጥ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑንና ለዚህም "ግልጽ ማስረጃዎች አሉ" ሲል አጸፋዊ ክስ ሰንዝሯል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም አይነት "ትንኮሳ" ለመመከት መንግስታቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኤርትራ መንግስት በበኩሉ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ህግጋትንና የቀጠናውን ሀገራት ሉዓላዊነት እየጣሰች ያለችው "የባህር በር ባለቤትነት" በሚል በምታሳየው የግዛት ማስፋፋት ፍላጎት ነው ብሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአንድ በኩል "ጥቃት አድራሽ" በሌላ በኩል ደግሞ "ተጠቂ" ሆኖ የመቅረብ ድራማ እየሰራ ነው ስትልም ወርፋለች።
በአጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለሀገር ውስጥ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትና ለክልላዊ ውጥረቶች ኤርትራንና ሕወሓትን ተጠያቂ ሲያደርጉ፤ የኤርትራ መንግስት ደግሞ በተቃራኒው የኢትዮጵያ መንግስት የሚከተለው "ያልተረጋጋና ቀስቃሽ" ፖሊሲ ለቀጠናው ሰላም መታወክ ዋና መንስኤ ነው የሚል አቋም ይዟል።
የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ በትግራይ ክልል ሰሞኑን ተባብሶ የቀጠለው አስገዳጅ ወታደራዊ አፈና በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቁ። ሚኒስትሩ በይፋ ባስተላለፉት መልዕክታቸው በትግራይ ክልል በተለይም በመ...
03/07/2026

ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ በትግራይ ክልል ሰሞኑን ተባብሶ የቀጠለው አስገዳጅ ወታደራዊ አፈና በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቁ።
ሚኒስትሩ በይፋ ባስተላለፉት መልዕክታቸው በትግራይ ክልል በተለይም በመቀሌና በተለያዩ ከተሞች እናቶች "ልጆቻችንን አትውሰዱብን" በማለት ተቃውሞ እያደረጉና መንገድ እየዘጉ እንደሚገኙ ገልጸው፣ ይህ የእናቶች እርምጃ ሊበረታታ ይገባል ብለዋል። ሚኒስትሩ ይህን ወታደራዊ አፈና እየፈጸሙ ያሉ አካላት ድርጊታቸውን እንዲያቆሙና በቅርቡ በዶ/ር ደብረጽዮን አማካኝነት የጸደቁት አፋኝ መመሪያዎች ሊወገዱ እንደሚገባም በመልዕክታቸው አመልክተዋል።

ዶ/ር አብርሃም በክልሉ የሚታየው ተቃውሞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ በተለይም የሚዲያ አካላት፣ የዲያስፓራ ማህበረሰብ፣ ወጣቶች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተቃውሞአቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው በሚስጥራዊ ስፍራዎች እገታዎች እንደሚፈጸሙና "ልጆቻችንን አሳልፈን አንሰጥም" ባሉ ሽማግሌዎችና ወላጆች ላይ እስር እየተፈጸመ መሆኑን በጽሁፋቸው ገልጸዋል። ይህን መሰሉ ህፃናትን አፍኖ ለሌላ ዓላማ አሳልፎ የመስጠት ድርጊት በአስቸኳይ ሊቆም እንደሚገባም አሳስበዋል።
የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

የአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ወደ መቀሌ ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ ለምን ተሰረዘ?አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ለማርገብና ዳግም ግጭት እንዳይ...
26/06/2026

የአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ወደ መቀሌ ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ ለምን ተሰረዘ?
አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ለማርገብና ዳግም ግጭት እንዳይከሰት ለማድረግ፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ለመወያየት በተደጋጋሚ ቀጠሮ ይዘው የነበረ ቢሆንም ለዛሬ ዓርብ ተይዞ የነበረውን ጨምሮ ጉዞው ሳይሳካ ቀርቷል። ለጉዞው መሰረዝ እንደ ምክንያት የቀረቡት፤ አንደኛው በህወሓት በኩል የሚፈለገው የውክልና እውቅና ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የፌደራል መንግሥት ያወጣው የውጭ ጉዳይ መመሪያ ነው።
አምባሳደር ኤርቪን ወደ መቀሌ ሲጓዙ ለማግኘት አቅደው የነበረው፣ በፌደራል መንግሥቱ ሥልጣናቸው የተራዘመውን ጀነራል ታደሰ ወረደን እንደ ክልሉ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት፣ እንዲሁም ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን እንደ ህወሓት ሊቀመንበርነት ነበር። ይህ የሆነው አምባሳደሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከዓመታት በፊት ያወጣውን መመሪያ ለመከተል በመፈለጋቸው ነው።

መመሪያው አምባሳደሮችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ያለ ቅድመ ማሳወቂያ ወደ ክልሎች እንዳይጓዙና ከክልል አመራሮች ጋር እንዳይገናኙ የሚከለክል ነው።
በዚህ መሠረት አምባሳደር ማሲንጋ ዶ/ር ደብረጽዮንን እንደ ህወሓት ሊቀመንበር፣ ጀነራል ታደሰ ወረደን ደግሞ እንደ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸው ያሳወቁ ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅት የክልሉን አስተዳደር ተቆጣጥረናል የሚሉት በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው አካል ግን እንደ ህወሓት ሊቀመንበር ሳይሆን እንደ ክልሉ መንግሥት ለመወያየት በመፈለጉና አምባሳደሩ ከጀነራል ታደሰ ወረደ ጋር እንዲገናኙ ባለመፍቀዱ ጉዞው ሳይሳካ ቀርቷል።
ይህንን ውይይት ለማድረግ ተደጋጋሚ ሙከራዎች ተደርገው ለመጨረሻ ጊዜ የተያዘው ቀጠሮ ለዛሬ ዓርብ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ነበር። ይሁን እንጂ ቀጠሮው ለጊዜው ባይሳካም፣ አምባሳደሩ በቀጣይ ለመወያየት የሚያደርጉትን ሙከራ እንደማያቋርጡ ተገልጿል።
የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

ጄኔራል ባጫ ደበሌ የአፍሪካ ህብረት የህወሓትን እርምጃ እንዲያወግዝ ጠየቁበቅርቡ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ ወደ ፕሬዝዳንትነት የተመለሱት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አሳሳቢ የተባለ አ...
25/06/2026

ጄኔራል ባጫ ደበሌ የአፍሪካ ህብረት የህወሓትን እርምጃ እንዲያወግዝ ጠየቁ
በቅርቡ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ ወደ ፕሬዝዳንትነት የተመለሱት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አሳሳቢ የተባለ አዋጅ በመላ ክልሉ ማወጃቸው ይታወሳል። ይህንኑ አዋጅ መመልከታቸውን የገለጹት በናይሮቢ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ፤ “የክተት አዋጅ እና የግዳጅ ምልመላ” በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ለጠቅላላ ጦርነት መቀስቀስ እንደሆነ አመልክተዋል።

ከዚህ ጦርነት ቀስቃሽ እንቅስቃሴ በስተጀርባ የራስን ጦር እንደገና ማጠናከር እና ታጣቂዎችን እንደ "ቅጥረኛ ተዋጊ" ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን ግጭት መላክ የሚሉ ግቦች እንዳሉ የገለጹት ጄኔራል ባጫ፤ የአፍሪካ ህብረት ይህን የህወሓት ድርጊት በአደባባይ እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም ህብረቱ ይህ አዋጅ በአስቸኳይ እንዲሰረዝ፣ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመለስና የፖለቲካ ሂደቶች እንዲቀጥሉ ግፊት እንዲያደርግ አምባሳደሩ አሳስበዋል። ሊፈጠር የሚችለውን አላስፈላጊ ቀውስ ለመከላከልም የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል።

የበለጠ መረጃ t.me/times_mereja_ethiopia

Address

Gonder

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Times መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share