27/03/2025
የሴቶች ቡድናችን በአሸናፊነቱ ቀጥሏል!
በሁለተኛው ዙር በመጀመሪያው የ14ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማን በማሸነፍ ዙሩን የጀመረው የሴቶች ቡድናችን ዛሬም በድል ቀጥሏል።
በ15ኛው ሳምንት ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚን ያስተናገደው ቡድኑ በቤቴልሄም ፍራኦል ሁለት ግቦች ታግዞ ማሸነፍ ችሏል።
ጥሩነሽ አካዳሚ 1-2 ወላይታ ድቻ
43' ጌጤነሽ ተስፋዬ | 26' ቤተልሔም ፍራኦል
40' ቤተልሔም ፍራኦል
🐝🐝 ድል ለጦና ንቦች 🐝🐝