19/12/2025
ምስኪኑ የፑል ኳስ❗❗❗
ይህ ዘማሪ ለአሕዛብ ጭምር በየሱስ ስም የሚያስብልና የፕሮቴስታንት ዕምነትን የሚያሰድብ ጭፈራና ያልተገባ ንግግር በመድረክ የሚጠቀም በመሆኑ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ስልጣን የተሰጣቸው አባቶች አገዱት። ይህ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ውሳኔ ሆኖ ሳለ ከቃለሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጋር እልህ የተጋባዉ ኢዩ ጩፋ ግን መሪዎችን ለማናደድ ብሎ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ጣሰ። ሰው ለማናደድ ከእግዚአብሔር ጋር ተላለፈ። በዚህ መሀል ይህ ዘማሪ መጠቀሚያው ሆነ። የራሱን ንዴት ሊወጣ እሱን ተጠቀመ። የሆነች የሻይ ወጪ ይሰጠው ይሆናል። የሆነ ፍርፋሪ ይወረውርለት ይሆናል። ነገር ግን ለሱ አስቦ ሳይሆን ለራሱ ብሎ ምስኪኑን በመድረክ አጃጃለው። ሰው እንዴት ሰውን ለማናደድ ከእግዚአብሔር ትዕዛዝ ጋር ይጋጫል።
ውድቀት ሲደርስ ትዕቢት ይቀድማል!!!