ካቶሊክ እምነት ብርሃን

08/07/2026

“ሕፃኑም አደገ፥ ጥበብም ሞልቶበት በመንፈስ ጠነከረ፤ የእግዚአብሔርም ጸጋ በእርሱ ላይ ነበረ።”
— ሉቃስ 2፥40

29/06/2026

፤ !!

✍️በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።
ዮሐንስ 3፥16

✍️አሁን ግን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ታይቶአል። እርሱ ሞትን ሽሮአልና እኔ ሰባኪና ሐዋርያ አሕዛብንም አስተማሪ እንድሆን በተሾምሁበት በወንጌል ሕይወትንና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን አውጥቶአል።
2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥10-11
ይህ አስተምዕሮ ነው።

# ጸጋ የትምህርት ርዕስ ሳይሆን ማንነት ነው፤ እርሱም ነው።

👉እኛ እውነትኛ አማኞች የዳነው #በጸጋ ነው፤ የሕይወታችን ለውጥም በዚው #ጸጋ ነው።

✍️በአጠቃላይ #ከጸጋው የተነጠለ ሕይወትም ኑሮም የለንም።

#ጸጋው ማንነታችን ነው።

✍️አንድ በእርግጠኛነት ይህንን #የጸጋ አስተምዕሮ በሙሉ ያመነና የተማረ እውነትኛ ክርስቲያን ኃጢአትን እንደፈለገ እያደረገና ልማዱ እያደረገ ፈጽሞ መኖር አይችልም።
ምክንያቱም ...👉

👉1ኛ ዮሐንስ 3፥9
ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኀጢአትን አያደርግም፤ የእርሱ ዘር በውስጡ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደም ኀጢአትን ሊያደርግ አይችልም።
1ኛ ዮሐንስ 3፥9 (አዲሱ መ.ት)

ሕያው ቃልን በደንብ አንብቡት ።

👉ቲቶ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
¹²-¹³ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤

✍️ይህ ማለት ደግሞ ፈጽሞ ሊደክም አይችልም ማለት እንዳልሆነ ግልጽ ነው ።

ነገር ግን ከዚህ ድካም ማምለጫው ደሞ :-

👉እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።
ዕብራውያን 4፥16
..በዚህ መንገድ ይወጣል።

👉 #በጸጋ ድነናል ፤ ለዘላለም አንጠፋም።
👉 #ጸድቀናል በኃጢአታችን አይደለንም።

Address

Sodo
SODO

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ካቶሊክ እምነት ብርሃን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share