E daily news Ethiopia

E daily news Ethiopia breaking news , sport ,news ,

በሁሉም የዓለም ዋንጫ የተሳተችፈው ብራዚል…ብራዚል በዓለም ዋንጫ መድረክ ከምስረታው ጀምሮ በእያንዳንዱ ውድድር ላይ በመሳተፍ ቀዳሚዋ እና ብቸኛዋ ሀገር ናት፡፡የዓለም ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀው...
12/06/2026

በሁሉም የዓለም ዋንጫ የተሳተችፈው ብራዚል…

ብራዚል በዓለም ዋንጫ መድረክ ከምስረታው ጀምሮ በእያንዳንዱ ውድድር ላይ በመሳተፍ ቀዳሚዋ እና ብቸኛዋ ሀገር ናት፡፡

የዓለም ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀው ትልቁ የሀገራት ውድድር የዓለም ዋንጫ በፈረንጆቹ 1930 ነው መደረግ የጀመረው፡፡

ብራዚል ከዓለም ዋንጫ ጅማሮ አንስቶ እስካሁን ድረስ በሁሉም የዓለም ዋንጫ የተሳተፈች ሲሆን ÷ የዘንድሮው ተሳትፎዋ ደግሞ ለተከታታይ 23ኛ ጊዜ ነው፡፡

በዚህም ብራዚል በሁሉም የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ በመሳተፍ እና በተከታታይ ለበርካታ ጊዜ በመድረኩ በመገኘት ቀዳሚዋ ሀገር ናት፡፡

በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብራዚል አምስት ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ቀዳሚ ብሔራዊ ቡድን ስትሆን ÷ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያሳካችው በፈረንጆቹ 1958 ነበር፡፡

በመቀጠልም በፈረንጆቹ 1962 ሻምፒዮን በመሆን በተከታታይ ዋንጫውን አሳክታለች፡፡ ከተጨማሪም በ1970፣ 1994 እና 2002 ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ አምስት ጊዜ ዋንጫውን በማሳካት ቀዳሚ ናት፡፡

ሆኖም ግን የአምስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊዋ ሀገር ብራዚል በፈረንጆቹ 2014 እራሷ ባዘጋጀችው መድረክ በጀርመን የደረሰባት ሽንፈት የሚረሳ አይደለም፡፡

በወቅቱ ብራዚል በእራሷ ድግስ በጀርመን ብሔራዊ ቡድን አስከፊ የ7 ለ 1 ሽንፈት ማስመዝገቧ ይታወሳል፡፡

ብራዚል ኔይማር ጁኒየርን በሩብ ፍጻሜው በከባድ ጉዳት ማጣቷን ተከትሎ ያለ ወሳኝ ተጫዋቿ ነበር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታውን ያደረገችው፡፡

ብራዚል በ2014ቱ የዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው በጀርመን ያልጠበቀችው ሽንፈት ማስተናገዷ የሚታወስ ነው፡፡

በስታዲየሙ የታደሙ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች በጭንቀት ተውጠው እና በእንባ ታጅበው ተመሳስሎ የተሰራውን ዋንጫ አቅፈው ጨዋታውን መመለከታቸው አይዘነጋም፡፡

በወቅቱ ብሔራዊ ቡድኑን በአምበልነት እየመራ ወደ ሜዳ የገባው ዴቪድ ሉዊዝ በእንባ ታጅቦ ደጋፊዎቻቸውን ይቅርታ ጠይቋል፡፡

የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎችም የብሔራዊ ቡድናቸውን ማልያ መሬት ላይ በመጣል የረጋገጡ ሲሆን÷ ከዚያም አልፈው ማቃጠላቸው አይዘነጋም፡፡

ብራዚል በ2014 ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው በጀርመን የደረሰባት አስከፊ ሽንፈት በዓለም ዋንጫ ወድድር ከማይረሱ ክስተቶች መካከል አንዱ ሆኖ በታሪክ ይወሳል፡፡

ለመጨረሻ ጊዜ በፈረንጆቹ 2002 የዓለም ዋንጫን ያሳካችው ብራዚል ለ6ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የምታደርገው ጉዞ ይጠበቃል፡፡

በአሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ የሚመራው ብሔራዊ ቡድኑ ኔይማር ጁኒየርን በስብስቡ ውስጥ አካትቷል፡፡

ኦፕታ የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ያሳካል በሚል ባስቀመጠው ቅድመ ትንተና መሰረት ብራዚል 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

ብራዚል የ2026 ዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋን የፊታችን እሑድ ከሞሮኮ ጋር የምታደርግ ይሆናል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት የአፍሪቃ ቀንድ ልዩ ልዑክ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በቅርቡ የትግራይ ክልል ርዕሰ-መስተዳድርነታቸውን መልሰው ከተረከቡት ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ጋር መቐለ ዉስጥ ተወያዩ። ...
11/06/2026

የአፍሪካ ኅብረት የአፍሪቃ ቀንድ ልዩ ልዑክ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በቅርቡ የትግራይ ክልል ርዕሰ-መስተዳድርነታቸውን መልሰው ከተረከቡት ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ጋር መቐለ ዉስጥ ተወያዩ።

የ89 ዓመቱ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ወደ መቐለ የተጓዙት የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የተፈራረሙትን ግጭት የማቆም ሥምምነት አፈጻጸም የመከታተል ኃላፊነት የተጣለባቸውን ወታደራዊ ባለሙያዎች አስከትለው ነው።

የትግራይ ክልል ፕሬዝደንት ጽህፈት ቤት ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ኦባሳንጆ እና አብረዋቸው ከተጓዙ ልዑካን ተገናኝተው መነጋገራቸውን በፌስቡክ ፎቶግራፎች አስደግፎ ባሠራጨው መልዕክት አስታውቋል።

ከቅርብ ወራት ወዲሕ የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና የህወሓት ልዩነት እየተካረረ ነዉ። ህወሓት በጳጉሜ 2012 በተካሔደ ምርጫ የተቋቋመ የክልል ምክር ቤቱን ወደ ሥራ በማስመለስ ደብረፅዮን ርዕሰ-መስተዳድርነቱን እንዲረከቡ አድርጓል።

ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ "ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት የአፍሪካ ኅብረትን ጥረት እንዲደግፉ" በኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ ዳግም የተሾሙት ከአንድ ወር ገደማ በፊት ነበር። የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ከጥቅምት 2013 እስከ ጥቅምት 2015 የተካሔደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ግጭት በማቆም ሥምምነቱ እንዲገታ የአፍሪካ ኅብረትን አደራዳሪነት መርተዋል።

አንድ የግል መኪና ሰሌዳ ለማውጣት በጥቅሉ 59 ሺህ 400 ብር ይፈጃል።አዲስ የግል መኪና ሰሌዳ ለማውጣት እና ለመመዝገብ የሚጠየቁ ዝርዝር የክፍያ ተመኖችአዲስ የግል ተሽከርካሪ የሚገዙ ወይም...
11/06/2026

አንድ የግል መኪና ሰሌዳ ለማውጣት በጥቅሉ 59 ሺህ 400 ብር ይፈጃል።

አዲስ የግል መኪና ሰሌዳ ለማውጣት እና ለመመዝገብ የሚጠየቁ ዝርዝር የክፍያ ተመኖች

አዲስ የግል ተሽከርካሪ የሚገዙ ወይም ሰሌዳ ለማውጣት የሚፈልጉ ባለቤቶች ሊከፍሏቸው የሚገቡ የክፍያ ዝርዝሮች እና አጠቃላይ የገንዘብ መጠን ይፋ ሆኗል።

በዚሁ መሠረት አንድ የግል መኪና ባለቤት አዲስ ለመመዝገብ በዋናነት

1. ለግል መገልገያ ሰሌዳ
2. ለባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር (ሊብሬ)
3. ለተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ
4. ለዓመታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ፣ ምዝገባና ተለጣፊ ምልክት የሚሆኑ የክፍያ ዓይነቶችን መፈጸም ይኖርበታል።

የክፍያዎቹ አጠቃላይ ድምር ሲሰላ አምሳ ዘጠኝ ሺህ አራት መቶ ብር እንደሚሆን ከወጣው ይፋዊ ሰነድ ለመረዳት ተችሏል።

1. የግል መገልገያ ሰሌዳ :- 56000.00

2. የባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር ሊብሬ :-1200.00

3. የተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ :- 700.00

4. ዓመታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ፣
ምዝገባና ተለጣፊ ምልክት :- 1500.00

ድምር 59400.00
የገንዘብ ልክ በፊደል አምሳ ዘጠኝ ሺህ አራት መቶ ብር

Via Tikvah Ethiopia

በዓለም ዋንጫ ከታዩ ያልተጠበቁ ድሎች አንዱ - ካሜሩን ከአርጀንቲና ከ36 ዓመታት በፊት የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በዛሬዋ ዕለት በዓለም ዋንጫ ውድድር የማይረሳ ታሪክ ጽፈዋል፡፡በፈረን...
09/06/2026

በዓለም ዋንጫ ከታዩ ያልተጠበቁ ድሎች አንዱ - ካሜሩን ከአርጀንቲና

ከ36 ዓመታት በፊት የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በዛሬዋ ዕለት በዓለም ዋንጫ ውድድር የማይረሳ ታሪክ ጽፈዋል፡፡

በፈረንጆቹ 1990 ጣሊያን ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ አርጀንቲና እና ካሜሩን በሳን ሲሮ ስታዲየም ተገናኝተዋል፡፡

በወቅቱ ድንቅ ብቃት ላይ በነበረውና በዲያጎ አርማንዶ ማራዶና የሚመራው የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ለጨዋታው ቅድመ ግምት አግኝቷል፡፡

የእግር ኳስ ተንታኞችና ግምቶች ሁሉ ወደ አርጀንቲና ያመዘኑ ሲሆን ÷ ማንም ከአፍሪካ ለመጣው የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ቦታ አልነበረውም።

የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን በወቅቱ በዓለም ዋንጫ መድረክ አንድም ጨዋታ አሸንፎ አያውቅም፤ በ1982 ተሳትፎውም ሦስት የአቻ ውጤት አስመዝግቦ ነው የተመለሰው፡፡

ሆኖም የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች (የማይበገሩት አንበሶች) ወደ ጣሊያን የመጡት ለሽርሽር አልነበረም፤ ታሪክ ለመጻፍ እንጂ።

የመጀመሪያው አጋማሽ የሁለቱ ቡድኖች ፍልሚያ በጠንካራ ፉክክር 0 ለ 0 አቻ ተናቀቀ፡፡

በ61ኛው ደቂቃ ላይ ካሜሩናዊው ተጫዋች አንድሬ ካና ቢይክ በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናበተ።

በ10 ተጫዋቾች ማራዶናን እና አጋሮቹን መቋቋም የማይታሰብ ይመስል ነበር።

ሆኖም ፍራንሷ ኦማም ቢይክ ከቅጣት ምት የተሻገረለትን ኳስ በግንባሩ ገጭቶ በማስቆጠር ካሜሩንን መሪ ማድረግ ቻለ፡፡

ከግቧ መቆጠር በኋላ ሌላኛው ካሜሩናዊ ተጫዋች ቤንጃሚን ማሲንግ በቀይ ካርድ አይቶ ከሜዳ ተሰናበተ፡፡

ካሜሩን ጨዋታውን 1 ለ 0 ማሸነፍ የቻለች ሲሆን÷ ድሉም የአፍሪካ እግር ኳስ መልክ የቀየረ ነበር፡፡

ጨዋታው በዓለም ዋንጫ ታሪክ ውስጥ ከታዩ ታላላቅ ያልተጠበቁ ድሎች አንዱ ሆኖ በታሪክ ይወሳል፡፡

ድንቃ ድንቅ መረጃ ብራዚል አንዲት የ37 አመት እንስት  የ12 ዓመት ህጻን ልጅ መስላ  በጉዲፈቻ መልክ አሳዳጊዎች ጋር ሰትኖር መያዟ ብዙዎችን አሰገረመ ።በብራዚል የ37 ዓመቷ ሴት እንደ ል...
08/06/2026

ድንቃ ድንቅ መረጃ

ብራዚል አንዲት የ37 አመት እንስት የ12 ዓመት ህጻን ልጅ መስላ በጉዲፈቻ መልክ አሳዳጊዎች ጋር ሰትኖር መያዟ ብዙዎችን አሰገረመ ።

በብራዚል የ37 ዓመቷ ሴት እንደ ልጅ ስታወራ፣ የውሸት ስሞችን ትጠቀም እንደነበርም ተነግሯል ።

ልጃችን ካለ እድሜዋ ወፍራለች ያሉ ቤተሰብም ተጨንቀው የክብደት መቀነሻ መድሀኒት ሲሰጧት ነበር ተብሏል።

አንድ የቤተሰቡ የቅርብ ሰው የግለሰቧን እንቅስቃሴ በመመልከት ጥርጣሬ አድሮበት ለፖሊስ በሰጠው መረጃ መያዟም ነው የተነገረው ።

ከፖሊስ ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ ማጭበርበሯን ያመነች ሲሆን ከዚህ በፊት በተለያዩ የብራዚል ከተሞች ውስጥ ማጭበርበርን ብዙ ጊዜ እንዳከናወነችም ተናግራለች ።

ሴትየዋ እስክትታሰር ድረስ ለአንድ አመት ከሁለት ወር ጊዜ እንደ 12 አመት ህጻን ልጅ እንክብካቤ እየተደረገላት ስትኖር እንደነበረ ዘገባዎች አንስተዋል።

የሴትየዋ ትክክለኛ ዕድሜ አሁን በህክምና ባለሙያዎች ተረጋግጦ 37 አመቷ እንደሆነ ሲገለጽ ፖሊስ በግለሰቧ ላይ የማጭበርበር ክስ መመስረቱን ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል እና ኢራን አሁኑኑ ’መታኮስ’ ማቆም አለባቸው አሉ። ፕሬዚዳንቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባጋሩት ጽሑፍ አገራቱ እርስ በእርሳቸው መታኮስ እ...
08/06/2026

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል እና ኢራን አሁኑኑ ’መታኮስ’ ማቆም አለባቸው አሉ። ፕሬዚዳንቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባጋሩት ጽሑፍ አገራቱ እርስ በእርሳቸው መታኮስ እንዲያቆሙ ጠይቀዋል።

ሀገሬ ቲቪ አልታገደም!* የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በነፃ ያስተላልፋል   | የሀገሬ ቴሌቪዥን የዓለም ዋንጫን በቀጥታ የማስተላለፍ መብት ማግኘቱን ተከትሎ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮ...
01/06/2026

ሀገሬ ቲቪ አልታገደም!

* የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በነፃ ያስተላልፋል

| የሀገሬ ቴሌቪዥን የዓለም ዋንጫን በቀጥታ የማስተላለፍ መብት ማግኘቱን ተከትሎ ከቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ኢቢሲ ጋር በተያያዘ እገዳ ሊጣልበት ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ መሆኑን የጣቢያው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንዋይ ይመር ገለጹ።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ከታዲያስ አዲስ የሬዲዮ ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት የጣቢያው የስርጭት መብት ሙሉ በሙሉ ህጋዊ በሆነ መንገድ የተገኘ መሆኑን አስረድተዋል።

የስምምነቱን ህጋዊነት በተመለከተም ስርጭቱ የተገኘው የፊፋ ወኪል ከሆነው የፈረንሳዩ ኒው ወርልድ ቲቪ ኩባንያ ጋር በስዊዘርላንድ ህግ መሰረት አለምአቀፋዊ ውል በመፈረም በመሆኑ በሀገር ውስጥ የሚወሩ ወሬዎች ስምምነቱን ሊያስተጓጉሉ እንደማይችሉ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን አቋም በተመለከተም ከባለስልጣኑ ኃላፊዎች ጋር መነጋገራቸውንና ምንም አይነት እገዳን የሚጠቁም ደብዳቤም ሆነ ስሜት አለመኖሩን አረጋግጠዋል።

በሌላ በኩል ከቶጎ ሎሜ የመጡ የፊፋ የቴክኒክ ባለሙያዎች ለጣቢያው ሰራተኞች የስርጭትና የቴክኒክ ስልጠናዎችን ሰጥተው ማጠናቀቃቸውንና ጣቢያው ስርጭቱን ለመጀመር በሙሉ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በመጨረሻም ስፖርት አፍቃሪው ማህበረሰብና ስፖንሰር አድራጊ ድርጅቶች በማህበራዊ ሚዲያ በሚለቀቁ ላልተረጋገጡ ወሬዎች ሳይደናገጡ የሀገሬ ቲቪ በኢትዮሳት ሳተላይት አማካኝነት ጨዋታዎቹን በነፃ ወደ እያንዳንዱ ቤት እንደሚያደርስ ዋና ስራ አስፈፃሚው ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

#ጌጡ #ጌጡተመስገን

በጸጥታ ችግር ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች በዛሬው ዕለት አለመከፈታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል “በተወሰኑ ቦታዎች” የድምጽ መስጠት ሂደቱ...
01/06/2026

በጸጥታ ችግር ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች በዛሬው ዕለት አለመከፈታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል “በተወሰኑ ቦታዎች” የድምጽ መስጠት ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ የተቋረጠባቸው የምርጫ ጣቢያዎች እንዳሉም ቦርዱ ገልጿል።

ቦርዱ ይህን ያስታወቀው ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24፤ 2018 ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ በሰጠው መግለጫ ነው።

Via: ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

የታክቲክ ልዕልና በዳኑብ ወንዝ ዳርቻ፤ የአርቴታው ጠንካራ መዋቅር ወይስ የሉዊስ ኤንሪኬ ፈጣን ነጻነት ነገ ምሽት ማንን ያነግሳል?ታላቁን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ የምታስተናግደ...
29/05/2026

የታክቲክ ልዕልና በዳኑብ ወንዝ ዳርቻ፤ የአርቴታው ጠንካራ መዋቅር ወይስ የሉዊስ ኤንሪኬ ፈጣን ነጻነት ነገ ምሽት ማንን ያነግሳል?

ታላቁን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ የምታስተናግደው ታሪካዊቷና ውቧ ቡዳፔስት ከተማ፣ በዳኑብ ወንዝ ለሁለት ተከፍላ የራሷ የሆኑ ሁለት ተቃራኒ ውበቶችን ይዛለች።

እንደከተማዋ ሁሉ በፑሽካሽ አሬና ነገ ምሽት ሁለቱ ታላላቅ ክለቦችም ፍጹም የተለያየ ነገር ግን እጅግ የተራቀቀ የእግር ኳስ ፍልስፍናን ይዘው ወደ ሜዳ ይገባሉ።

ከተማዋ ኮረብታማ በሆነውና የጥንታውያን ነገሥታት መኖሪያ በነበረው "ቡዳ" እና ሰፊ የንግድ ማዕከል በሆነው ሜዳማው "ፔስት" እንደተዋቀረችው ሁሉ፣ የአሰልጣኞቹ የስትራቴጂ ፍልሚያም ይህንኑ ድንቅ ውህደት ይመስላል።

የአርሰናሉ ሚኬል አርቴታ የሚከተለው የጨዋታ ስልት፣ ልክ እንደ ጥንታዊው የቡዳ ክፍል ኮረብታዎች ጠንካራ፣ የማይናወጥ እና በከፍተኛ ጥንቃቄ የተገነባ መዋቅር አለው።

አርቴታ የአርሰናልን ማራኪ አጨዋወት ዛሬ ላይ ካለው ዘመናዊና የመከላከል ጥበብ ጋር በድንቅ ሁኔታ በማዋሃድ ቡድኑን ለትልቅ ክብር አጭቶታል።

በአንጻሩ የፒኤስጂው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤነሪኬ የሚያራምደው የጨዋታ ፍልስፍና ደግሞ ልክ እንደ ፔስት ሜዳማ ክፍል ሁሉ ሰፊ፣ ፈጣን፣ ነጻ እና በአጥቂዎች ልዩ ክህሎት ላይ የተመሠረተ ነው።

ፒኤስጂ የሜዳውን ስፋት ሙሉ በሙሉ በመጠቀም በተለይም በክንፍ መስመሮች ላይ ባሉት ፈጣን ኮከቦቹ አማካኝነት የተጋጣሚን ተከላካይ የማስጨነቅ ስልት አለው።

ያልተገደበ ነጻነትን ለአጥቂዎች የሚሰጠው የሉዊስ ኤነሪኬ ፈጣን ስልት፣ የአርሰናልን ጠንካራና የማይበገረውን መዋቅር ሰብሮ የራሱን አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ወደ ሜዳ ይገባል።

እነዚህ ሁለት የተለያዩ የአሰልጣኞች አስተሳሰቦች በዳኑብ ወንዝ ዳርቻ ፊት ለፊት ሲገናኙ የምሽቱን ጨዋታ እጅግ አስደናቂና ማራኪ ያደርጉታል ተብሎ ይጠበቃል።

በጥንካሬና በነጻነት መካከል የሚደረገው ይህ ታላቅ ፍልሚያ የማንን ፍልስፍና የአሸናፊነት አክሊል እንደሚያቀዳጅ ለማየት መላው ዓለም ነገ ምሽት የሚደረገውን የሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ በከፍተኛ ጉጉት እየተጠባበቀ ይገኛል።

በሀብተሚካኤል ክፍሉ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፤ የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ጋዛ ውስጥ የሚቆጣጠረውን የግዛት ስፋት ወደ 70 በመቶ እንዲያሳድግ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ገለጹ።
29/05/2026

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፤ የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ጋዛ ውስጥ የሚቆጣጠረውን የግዛት ስፋት ወደ 70 በመቶ እንዲያሳድግ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ገለጹ።

Address

Jimma

Telephone

+251928348206

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when E daily news Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to E daily news Ethiopia:

Share