25/08/2026
😭😭 #የሀዘንመግለጫ😭
የደ ብርሃን ከተማን እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለብዙ ዓመታት በትጋትና በታማኝነት ሲመሩ የቆዩት እንዲሁም የደብረብርሃን ከተማ ተስፋ ብርሃን የስፓርት ባለሙያዎች ማህበር መስራችና ፀሀፊ የመምህር ቻለው ኃይሌ ልጅ የሆነው ወጣት ዩሃንስ ቻለው በድንገተኛ አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶናል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ተስፋ ብርሃን ስፖርት ባለሙያዎች ማህበር በወጣት ዩሃንስ ቻለው ድንገተኛ ህልፈት የተሰማንን እጅግ ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለወንድማችን ለአቶ ቻለው ሀይሌ እና መላው ቤተሰቡ፣ ዘመዶቹ፣ ወዳጆቹ ከልብ የሆነ መጽናናትን እንመኛለን።
እግዚአብሔር ነፍሱን በሰላም ያኑር፤ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ ሁሉ መጽናናቱን ይስጥ።
ተስፋ ብርሃን የስፓርት ባለሙያዎች ማህበር !!
ደብረ ብርሃን