08/09/2026
✍️ ምርጦችን ብቻ በአንድ መድረክ የሚያፋልመው ውድድር!!
የዓለም አትሌቲክስ አዲስ ውድድር የሆነው የዓለም አትሌቲክስ አልቲሜት ሻምፒየንሺፕ World Athletics Ultimate Championship 2026 ውድድር የፊታችን አርብ በሃንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስትይጀምራል።
በአይነቱ ለየት ያለ እና ምርጦችን ብቻ በመድረኩ የሚያገናኝ አዲሱ ውድድር በፈረንጆቹ ከመስከርም 11 እስከ 13 የሚደረግ ሲሆን ሽልማቱም እጅግ ከፍ ያለ እና የአለም አትሌቲክስ በእስካሁን እድሜ ቆይታው ለአሸናፊዎች ሸልሞት የማያውቀው ውድድር ነው፡፡
ይህ ውድድር አትሌቶች በየውድድር አይነቱ ባላቸው ፈጣን ሰዓት እና ከዚህ ቀደም በፓሪስ ኦሊምፒክ እና በዓለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ የሆኑት የሚፋለሙበት ነው።
ሀገርን ወክለው ጠቀም ያለ ሽልማት የሚያገኙበት ይህ ውድድር በአትሌቶች ኮታ ሳይሆን በሚወዳደሩበት ርቀት ባላቸው ጥሩ ሰዓት በርካታ አትኬቶች መሳተፍ የሚችሉበት ነው።
በኢትዮጵያ አዲስ ዓመት 150,000 ዶላር የሚያሸልም ታላቅ የዓለም አቀፍ ውድድር ይዘጋጃል።
የትራክ እና የሜዳ ላይ ተግባራትን አካቶ በ28 የውድድር አይነቶችን የተከሰተው ሻምፒየንሺፑ ቀዳሚ ሆኖ ላጠናቀቁ አትሌት 150ሺ ዶላር ይሸልማል።
ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ለሚያጠናቅቀው አትሌት 75ሺ ዶላር እና ሶተኛ ለሚወጣው አትሌት 40ሺ ዶላር ሽልማት ሸልማለው ሲል የዓለም አትሌቲክስ ይፋ አድርጓል።
ለተከታታይ ሶስት ቀናቶች በሚደረገው ውድድሩ በመድረኩ ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ተለይተው ታውቀዋል።
ፅጌ ዱጉማ እና ንግስት ጌታቸው በ800 ሴቶች ሀገራቸውን ወክለው ጠቀም ያለ ሽልማት ለመውሰድ ይፋለማሉ፡፡
በሴቶች 1ሺ 500 ሜትር በሚደረገው ፉክክር
በርቀቱ ተደጋጋሚ ጊዜ ያሸነፈቸውን ብርቄ ሀይሎምን ጨምሮ ሳሮን በርሄ፣ ፍሬወይኒ ሀይሉ እና ወጠቷ ሀረገወይኒ ካላዩ ለማሸነፍ ይፋለማሉ፤
ሌላኛው በ5ሺ ሜትር ሴቶች የአለም አትሌቲክስ የመረጣቸው ኢትዮጵያኑ አትሌቶች መዲና ኢሳ፣ፍሬወይኒ ሀይሉ፣ ልቅና አምባው፣አለሽኝ ባወቀ፣ሰናይት ጌታቸው እና ፋንታዬ በላይነህ
በተመሳሳይ ርቀት በወንዶች 5ሺ በሚደረገው ውድድር የአመቱ ፈጣን ሰዓት ባለቤት የሆነው
አትሌት አዲሱ ይሁኔን ጨምሮ ወጣቱ ቢንያም መሀሪ እነደሚካፈል የዓለም አትሌቲክስ ያወጣው መረጃ ያሳያል፡፡
የሃንጋሪ ዋና ከተማዋ የሆነችው ቡዳፔስት ከ19ኛ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 2023 በኋላ ይምታዘጋጀው ትልቅ የውድድር መድረክ ነው።