21/05/2026
የኢትዮጵያ ከ 17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ወደ ዓለም ዋንጫ ለማለፍ የመለያ ጨዋታውን በመጪው ቅዳሜ ከሞዛምቢክ ጋር ያደርጋል
ቡድኑ ቱኒዚያን በማሸነፍ ከምድብ ሀ ሦስተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ የሚታወስ ሲሆን በውድድሩ ደንብ መሰረት የመለያ ጨዋታ (Playoff) የምድብ ሐ 3ኛ ደረጃ ይዞ ካጠናቀቀው ሞዛምቢክ ብሔራዊ ቡድን ጋር በመጪው ቅዳሜ ግንቦት 15 ከምሽቱ 1:00 ያከናውናል።
ይህን ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ በኳታር አስተናጋጅነት ለሚከናወነው የ2026 ከ17 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ የሚያልፍ ይሆናል።