20/05/2026
አስቶንቪላ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ
አስቶንቪላ ፍሬይቡርግን 3ለ0 በማሸነፍ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫ አሸናፊ መሆኑን አረጋገጠ።
በቤሺክታሽ ፓርክ በተደረገው ጨዋታ የእንግሊዙን ክለብ ድል ያበሰሩ ግቦች ዩሪ ቲሊማንስ ፣ ኤሚ ቡንዲያ እና ሞርጋን ሮጀርስ አስገኝተዋል።
የአስቶንቪላን የበላይነት መግታት ያልቻለው የጀርመኑ ክለብ ፍሬይቡርግ የመጀመሪያ የአውሮፓ ውድድር የፍፃሜ ጨዋታው በሽንፈት ተደምድሟል።
አስቶንቪላ በአውሮፓ መድረክ ሲነግስ ከ44 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ቪሊ እኤአ ከ1982 ባየርን ሙኒክን አሸንፎ የዩሮፒያን ካፕ (አሁን ቻምፒየንስ ሊግ) ካሸነፈ በኋላ ዋንጫ የማንሳት እድል አልነበረውም።
"የዩሮፓ ሊግ ንጉስ" የሚል ቅፅል ስም ያገኙት የአስቶኝቪላው አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬይ አምስተኛ ዋንጫቸውን አንስተዋል። ስፔናዊው አሰልጣኝ ከዚህ ቀደሞ ከሲቪያ ጋር ሦስት ፣ ከቪያሪያል ጋር ደግሞ አንድ ጊዜ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ማሸነፋቸው ይታወቃል።