15/05/2026
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በማሸነፍ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ስታዲየም ሊቨርፑልን ያስተናገደው አስቶን ቪላ ሮጀርስ፣ ዋትኪንስ (ሁለት) እና ማክጊን ባስቆጠሯቸው ግቦች ድል አድርጓል።
የሊቨርፑልን ግቦች ቫን ዳይክ ከመረብ አሳርፏል።
በዚህም አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ ሁለተኛ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ሊቨርፑል በ59 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።