06/01/2026
ቼልሲ በይፋ አሰልጣኝ ሾመ
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ እንግሊዛዊውን አሰልጣኝ ሊያም ሮሴንየር እንደ አዲስ ዋና አሰልጣኝ መሾሙን በይፋ አሳውቋል።
ሮሴንየር እስከ 2032 ድረስ የሚቆይ የስድስት ዓመት ውል ከክለቡ ጋር ፈርመዋል።
ከፊርማው ቡኋላ “ቼልሲን ተፎካካሪ እና በትልቅ ደረጃ አሸናፊ ቡድን ለማድረግ በየቀኑ ያለኝን ሁሉ እሰጣለሁ” ብለዋል።