08/01/2026
ለመገናኛ ብዙሃን !
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን መሾማቸው ይታወቃል። የውሉን ዝርዝር እና አጠቃላይ ጉዳዮች በተመለከተ ሐሙስ ታኅሣሥ 30 ቀን 2018 ዓ/ም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፅሕፈት ቤት ከቀኑ በ9፡00 ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
የመገናኛ ብዙሃን አካላትም በቦታው በመገኘት ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ እና የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡ በማክበር እንጠይቃለን፡፡