11/08/2025
በክለባችን እና ዶናሩማ መካከል ያለው ሁኔታ?
ክለባችን የዶናሩማን ጉዳይ ጠንቅቆ እንደሚያውቅና እንደሚከታተል ተገልጿል።
ሆኖም ክለባችን በዝውውሩ ዙሪያ እስካሁን ይሄ ነው የሚባል ተጨባጭ ደረጃ ላይ መድረሱን የሚያመላክቱ ሁነቶች አለመኖራቸው ተዘግቧል።
ክለባችን አሁናዊ ትኩረቱ በሽያጭና የባሌባ ዝውውር ላይ መሆኑ ተጠቁሟል።
በአሁኑ ሰዓትም ክለባችን ከግብጠባቂ ይልቅ አማካይ የማስፈረም እድሉ ሰፊ እንደሆነ ላውሪ ዊትዌል ዘግቧል።
ከደቂቃዎች በፊት ይኸው የፔዤ የግብ ዘብ ከአውሮፓ ሱፐር ካፕ የቡድን ስብስብ ውጪ መደረጉና 100% ይለቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ መዘገቡ አይዘነጋም።
ይህንኑ የዶናሩማ ከስብስብ ውጪ መደረግ ከሌሎቹ ምንጮች ቀድሞ ያሳወቀውም ፋብሪዚዮ አያይዞም የግብጠባቂው ምርጫ ፕሪሚየር ሊግ መሆኑን ጠቁሟል።