Ethiopian wheelchair Basketball Association

Ethiopian wheelchair Basketball Association Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian wheelchair Basketball Association, Sports, Addis Ababa.

በ6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታ አንዱ የስፖርት አይነት የነበረው የዊልቼር ቅርጫት ኳስ ውድድር በዛሬው እለት ፍጻሜውን አግኝቷል። በውድድሩም በወንድም በሴትም የአዲስአበባ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ ቡ...
23/06/2025

በ6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታ አንዱ የስፖርት አይነት የነበረው የዊልቼር ቅርጫት ኳስ ውድድር በዛሬው እለት ፍጻሜውን አግኝቷል።
በውድድሩም በወንድም በሴትም የአዲስአበባ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ ቡድን ሻምፒዩን (አሸናፊ) መሆን ችሏል። እንዲሁም አማራ ክልል በወንድ 2ኛ በሴት 3ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል። በተመሳሳይ ኦሮሚያ በሴት 2ኛ በወንድ 3ኛ ሆኖ ውድድሩን ሲያጠናቅቅ ድሬዳዋ በወንድ በሴት እንዲሁም ትግራይ በወንዶች ተሳታፊ ሆነዋል።
በወንዶች የፍጻሜ ጨዋታውን የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ክቡር አቶ አንበሳው እንየው እና የዊልቼር ቅርጫት ኳስ የስራ አስፈጻሚ አባላት ተገኝተው ውድድሩን ተመልክተዋል በመልዕክታቸውም የስራ አስፈጻሚ አባላትን አመስግነዋል ስፖርተኞቹንም አበረታተዋል።

ሰኔ 16/2017 ዓ.ም
ጅማ

የዛሬ የጨዋታዎች ውጤት እና የነገ የጨዋታዎች ፕሬግራምከጅማ
21/06/2025

የዛሬ የጨዋታዎች ውጤት እና የነገ የጨዋታዎች ፕሬግራም
ከጅማ

የኢትዮጵያ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ አሶሴሽን 6ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ አካሄደሰኔ 13/ 2017 ዓ. ም ጅማአሶሴሽኑ 6ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጅማ ከተማ አካሂዷል በጉባኤውም 7 ክልሎች ...
20/06/2025

የኢትዮጵያ ዊልቼር ቅርጫት ኳስ አሶሴሽን 6ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ አካሄደ
ሰኔ 13/ 2017 ዓ. ም ጅማ
አሶሴሽኑ 6ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጅማ ከተማ አካሂዷል በጉባኤውም 7 ክልሎች እና 2 ከተማ መስተዳደሮች በተወካዮቻቸው ተሳታፊ ሁነዋል::
በጉባኤውም በሚከተሉተ አጀንዳዎቸ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገ በኋላ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል
1. የፋይናንስ መመሪያ ማሻሻያ
2. የ4 አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ
3. የሁለት አመት የፋይናንስ ሪፖርት
4. የ2017 ዓ.ም ሪፖርት
5. የ2018ዓ.ም ዕቅድ
በተጨማሪም አዳዲስ ክልሎች የአባልነት ጥያቄ አቅርበው ተቀባይነተ አግኝተዋል::

Today's Game Result and Tomorrow Program!!
20/06/2025

Today's Game Result and Tomorrow Program!!

6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታ የዊልቼር ቅርጫት ኳስ ውድድር የዛሬ ውጤት እና ቀጣይ ፕሮግራም
19/06/2025

6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታ የዊልቼር ቅርጫት ኳስ ውድድር የዛሬ ውጤት እና ቀጣይ ፕሮግራም

በ6ኛው የኢትዮጵያ መላ ጨዋታዎች ላይ የዊልቼር ቅርጫትኳስ ውድድር አንዱ ሆኖ እየተካሄደ ይገኛል። 6ኛው የኢትዮጵያ መላ ጨዋታ በጅማ ከተማ በርካታ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣የስፖርት ቤተሰ...
19/06/2025

በ6ኛው የኢትዮጵያ መላ ጨዋታዎች ላይ የዊልቼር ቅርጫትኳስ ውድድር አንዱ ሆኖ እየተካሄደ ይገኛል።

6ኛው የኢትዮጵያ መላ ጨዋታ በጅማ ከተማ በርካታ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣የስፖርት ቤተሰቦች እና ስፖርተኞች በተገኙበት ሰኔ 10/2017 ዓ.ም በደመቀ ሁኔታ የመክፈቻ ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን በዛሬው ዕለት ውድድሮች በተለያዩ የስፖርት ማዝውተሪያ ስፍራዎች ብዙ ተመልካች በተገኘበት መካሄድ ጀምሯል።

የዊልቼር ቅርጫትኳስ ስፖርትም በወንዶች 5 በሴቶች 4 ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች ተሳታፊ ሆነው ዛሬ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ጅምናዚየም ውስጥ የመጀመሪያ ቀን 4 ጨዋታዎች ተካሂደዋል። በዕለቱ የአሶሴሽኑ ስራ አስፈጻሚዎች በቦታው በመገኘት ውድድሩን ታድመዋል ተሳታፊ ክልሎችንም አበረታተዋል።

12/10/2017 ዓ.ም ውጤት

በወንድ
ኦሮሚያ 10-5 ድሬዳዋ
ትግራይ 10-38 አዲስአበባ

በሴት
ኦሮሚያ 5-16 አዲስአበባ
አማራ 24-0 ድሬዳዋ

የ13/10/2017 ፕሮግራም

በወንድ
ድሬዳዋ ከ አማራ
ኦሮሚያ ከ ትግራይ

በሴት
አዲስአበባ ከ አማራ
ድሬዳዋ ከ ኦሮሚያ

#ስፖርተኞችን በቦታው በመገኘት እንድታበረታቱ እና በውድድሩ እንድትዝናኑ ተጋብዛችኋል።
#ጅማ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ባለው ጅምናዚየም።

10/06/2025
Are you ready?
10/06/2025

Are you ready?

22/09/2024

አስቸኳይ አስቸኳይ አስቸኳይ
==================
እንዴት ከረማችሁ? እንዴት ሰነበታችሁ? የዊልቼር ቅርጫት ኳስ ቤተሰቦች!
ሊቢያ ከ23 አመት በታች በወንዶች የዊልቼር ቅርጫት ኳስ ሻምፒዮና ጥር ወር ላይ ታዘጋጃለች። ከተሳካልን (በጀት ከተፈቀደ) ልንሳተፍ ፈልገናል እና
#ፓስፖርት ያላችሁ እድሜያችሁ (የፓስፖርት) ከ23 አመት በታች የሆናችሁ በውስጥ መስመር
#የፓስፖርታችሁን ፎቶ ላኩልኝ።
#መልካም ቀን

22/06/2024

With Wheelchair Basketball Federation of India - WBFI – I just got recognized as one of their top fans!

22/06/2024

With IWBF Africa – I just got recognized as one of their top fans!

Address

Addis Ababa

Telephone

+251913998204

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian wheelchair Basketball Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category