10/03/2026
ነገ በሻንፒየንስ ሊጉ ከሜዳ ውጪ ከባየርሊቨርኩሰን ጋር ለምናደርገው ጨዋታ ዛሬ የአርሰናል ተጨዋቾች ልምምዳቸውን በሚያምር መልኩ ጥርስ በጥርስ ሆነው አከናውነዋል።
ትሮሳርድ እና ካላፊዮር በኤፍኤካፑ በጉዳት ተቀይረው የወጡ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ከቡድኑ ጋር ልምምዳቸውን በሚገባ አከናውነዋል፣ ዊልያም ሳሊባም ገጥሞት ከነበረው የቁርጭምጭሚት ህመም ሙሉ በሙሉ አገግሞ ትሬኒንጉን በሚገባ ሰርቷል፣ ወጣቶቹ ዶውማን እና ሳልሞን ዛሬም ከቡድኑ ጋር ልምምድ አድርገዋል።
በዛሬው ልምምድ ኦዴጋርድና ቤን ዋይት አልታዩም ከእነሱ ውጪ ያሉት በሙሉ ዝግጁ ናቸው።