10/05/2026
ድንበር ላይ ውጊያ ተቀስቅሷል‼️
የሱዳኑ ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተስፋፋ መሆኑን የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል።
የሱዳን መንግሥት በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ፈፀምኩት ባለው ጥቃት ሁለት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ካምፖችን ከጥቅም ውጪ ማድረጉን አሳውቋል።
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦርም በርካታ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል።
ለኢትዮጵያ ቅርብ በሆነው የሱዳን ብሉናይል ግዛት ከባድ ውጊያ እየተደረገ ይገኛል። ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ እና የሱዳን ጦር ስትራቴጂክ ስፍራዎችን ለመቆጣጠር እየተጋደሉ ነው።
በውጊያው SPLMO ተብሎ የሚጠራው የደቡብ ሱዳን አማጺ ከሄሜቲ ጦር ጋር ተሰልፏል።
በተጨማሪ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከአሶሳ በኩል ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የሱዳን ምንጮች ዘግበዋል።
የሱዳን መንግሥት ከትናንት በስተያ ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ተጨማሪ ጦር እና መሳሪያ መላኩን መዘገባችን ይታወሳል።
(አዩዘሀበሻ)
=====================
💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s